ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዘንድሮ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ከ420 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት እንደሚለማ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በልማት ስራው ከ2 ሚሊየን 600 ሺህ በላይ ህዝብ እንደሚሳተፍም ተጠቁሟል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ በጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጋንታ መይጨ ቀበሌ “በተደራጀ የህዝብ ንቅናቄ የሚፈፀም የተቀናጀ ተፋስ ልማት ለሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የክልሉ ቢሮ ኃላፊን ጨምሮ የቢሮ ማኔጅመንት አባላትና የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች በተገኘበት በይፋ ተጀምሯል።
በተፋሰስ ልማት ስራ ባለፉት አመታት የተቀመሩ ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት ንዑስ ተፋሰሶችን ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ አድርጎ መልማት እንዳለበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃ/ማሪያም ተስፋዬ አሳስበዋል።
ለተከታታይ 30 ቀናት በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የሚተገበረው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ለተራራ ልማትና ለጠረጴዛማ እርከን ስራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ተጠቁሟል።
ዘጋቢ፡ ሰናይት ካሳ

More Stories
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
በዘመናዊ የእንስሳት እርባታ ዘርፍ በመሰማራታቸው የቤት ፍጆታን ከማሟላት ባሻገር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን በጋሞ ዞን ገረሴ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ አንዳንድ አካላት አረጋገጡ