ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቡርጂ ዞን የሶያማ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተደራሽነትን ለማፋት እየሠራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር በማህበራዊ ክላስተር የጤና ዩኒት አስተባባሪ አቶ ኮሹ ሁቃ በከተማ አስተዳደር ስር ባሉ 6 ቀበሌያት የሚኖሩ የማህበረሰብ አካላትን ያካተተ 1ሺህ 7 መቶ 43 በራሳቸው ከፍለው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡
መንግስት ወጪ የሚሸፍንላቸው 3 መቶ 32 ነዋሪዎች ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ 2 ሺህ 74 ዜጎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል ብለዋል፡፡
ዩኒቱ መታወቂያ ያገኙ ቤተሰቦች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሶያማ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ጋር ውል መግባቱን ኃላፊው ተናግረዋል።
የተቀሩት የህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
በከተማው ጤና ኤክስተንሽን ሙያተኛ ሲስተር ስመኙሽ አለማየሁ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ከአጠቃቀም አንፃር የግንዛቤ ችግር እንዳለባቸው በማንሳት በተለይም ውል ከተገባበት ጤና ተቋም ውጪ አገልግሎት የመጠየቅ ሁኔታዎች መኖራቸውን አንስተዋል።
ወ/ሮ ስሌ አያና እና ቦጋለች ጫንያለው በጋራ በሰጡን አስተያየት የማህበረሰብ ጤና መድን አገልግሎት በርካታ ጥሩ ነገሮች ያሉት መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ : አብዶ አያላ- ከይ/ጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው
የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመመለስ በኩል ከመንግስት ጥረት ባለፈ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና የጎላ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ተናገሩ
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናን አስጀመሩ