ሀዋሳ፡ ጥር 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቡርጂ ዞን የሶያማ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተደራሽነትን ለማፋት እየሠራ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡
በቡርጂ ዞን ሶያማ ከተማ አስተዳደር በማህበራዊ ክላስተር የጤና ዩኒት አስተባባሪ አቶ ኮሹ ሁቃ በከተማ አስተዳደር ስር ባሉ 6 ቀበሌያት የሚኖሩ የማህበረሰብ አካላትን ያካተተ 1ሺህ 7 መቶ 43 በራሳቸው ከፍለው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡
መንግስት ወጪ የሚሸፍንላቸው 3 መቶ 32 ነዋሪዎች ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ 2 ሺህ 74 ዜጎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል ብለዋል፡፡
ዩኒቱ መታወቂያ ያገኙ ቤተሰቦች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሶያማ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ጋር ውል መግባቱን ኃላፊው ተናግረዋል።
የተቀሩት የህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
በከተማው ጤና ኤክስተንሽን ሙያተኛ ሲስተር ስመኙሽ አለማየሁ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ከአጠቃቀም አንፃር የግንዛቤ ችግር እንዳለባቸው በማንሳት በተለይም ውል ከተገባበት ጤና ተቋም ውጪ አገልግሎት የመጠየቅ ሁኔታዎች መኖራቸውን አንስተዋል።
ወ/ሮ ስሌ አያና እና ቦጋለች ጫንያለው በጋራ በሰጡን አስተያየት የማህበረሰብ ጤና መድን አገልግሎት በርካታ ጥሩ ነገሮች ያሉት መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ : አብዶ አያላ- ከይ/ጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ