በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ ወረዳ የ2016 ዓ.ም የተፋሰስ ልማትና የበልግ ሥራዎች ንቅናቄ በሃና ከተማ ተካሄዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካድሱ ካሻሌ እንደገለፁት፤ የተፋሰስ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፤ ብዝሃ ሀብቶችን ለማስጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እንደሚረዳ ገልፀው በእስከዛሬው ሂደትም የአርሶ አርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ለወጥ ያመጣ እንደሆነ አመላክተዋል።
አክለውም የሥነ-አካላዊ እና ሥነ-ህይወታዊ ሥራዎችን በማጠናከር በተያያዘም የበልግን ሥራ በውጤታማነት ለመፈፀም ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲረባረቡም አሳስበዋል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የተፋሰስ ልማት ጥናትና ዲዛይን ባለሙያ አቶ ያንተአለ ላቀው በዘንድሮ 2016 ዓ.ም የተፋሰስ ልማት ሥራ አጠቃላይ 32ሺህ አባወራ፣ እማወራ እና ወጣቶችን በማሳተፍ 24ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልፀዋል።
በመድረኩም መነሻ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሄዶበታል።
ከተሣታፊዎች መካከል አቶ ሉች ናበጋስ ፤ ጌታሁን ማሞ እና ሌሎችም በሰጡት አሰተያየት ከዚህም ቀደም በነበሩ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ምርታማነታቸው እንደጨመረ ገልፀው በዘንድሮውም በተሻለ መንገድ ለመስራት በንቅናቄ ተሳትፈው እንደሚያሳትፉ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ደፋሩ ስፍታዬ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ