በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ ወረዳ የ2016 ዓ.ም የተፋሰስ ልማትና የበልግ ሥራዎች ንቅናቄ በሃና ከተማ ተካሄዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካድሱ ካሻሌ እንደገለፁት፤ የተፋሰስ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፤ ብዝሃ ሀብቶችን ለማስጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እንደሚረዳ ገልፀው በእስከዛሬው ሂደትም የአርሶ አርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ለወጥ ያመጣ እንደሆነ አመላክተዋል።
አክለውም የሥነ-አካላዊ እና ሥነ-ህይወታዊ ሥራዎችን በማጠናከር በተያያዘም የበልግን ሥራ በውጤታማነት ለመፈፀም ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲረባረቡም አሳስበዋል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የተፋሰስ ልማት ጥናትና ዲዛይን ባለሙያ አቶ ያንተአለ ላቀው በዘንድሮ 2016 ዓ.ም የተፋሰስ ልማት ሥራ አጠቃላይ 32ሺህ አባወራ፣ እማወራ እና ወጣቶችን በማሳተፍ 24ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልፀዋል።
በመድረኩም መነሻ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሄዶበታል።
ከተሣታፊዎች መካከል አቶ ሉች ናበጋስ ፤ ጌታሁን ማሞ እና ሌሎችም በሰጡት አሰተያየት ከዚህም ቀደም በነበሩ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ምርታማነታቸው እንደጨመረ ገልፀው በዘንድሮውም በተሻለ መንገድ ለመስራት በንቅናቄ ተሳትፈው እንደሚያሳትፉ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ደፋሩ ስፍታዬ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአለም አቀፉን ተለዋዋጭ ሁኔታ በአግባቡ ለይቶ የሀገር ውስጥ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወልቂጤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ