በደቡብ ኦሞ ዞን ሣላማጎ ወረዳ የ2016 ዓ.ም የተፋሰስ ልማትና የበልግ ሥራዎች ንቅናቄ በሃና ከተማ ተካሄዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካድሱ ካሻሌ እንደገለፁት፤ የተፋሰስ ልማት የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፤ ብዝሃ ሀብቶችን ለማስጠበቅ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር እንደሚረዳ ገልፀው በእስከዛሬው ሂደትም የአርሶ አርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ለወጥ ያመጣ እንደሆነ አመላክተዋል።
አክለውም የሥነ-አካላዊ እና ሥነ-ህይወታዊ ሥራዎችን በማጠናከር በተያያዘም የበልግን ሥራ በውጤታማነት ለመፈፀም ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲረባረቡም አሳስበዋል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የተፋሰስ ልማት ጥናትና ዲዛይን ባለሙያ አቶ ያንተአለ ላቀው በዘንድሮ 2016 ዓ.ም የተፋሰስ ልማት ሥራ አጠቃላይ 32ሺህ አባወራ፣ እማወራ እና ወጣቶችን በማሳተፍ 24ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ገልፀዋል።
በመድረኩም መነሻ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሄዶበታል።
ከተሣታፊዎች መካከል አቶ ሉች ናበጋስ ፤ ጌታሁን ማሞ እና ሌሎችም በሰጡት አሰተያየት ከዚህም ቀደም በነበሩ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ምርታማነታቸው እንደጨመረ ገልፀው በዘንድሮውም በተሻለ መንገድ ለመስራት በንቅናቄ ተሳትፈው እንደሚያሳትፉ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ደፋሩ ስፍታዬ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ