የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት 13ኛ ዓመት 1ኛ ዙር መደበኛ ጉባኤው ማካሔድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ጥር 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ግድባችን፤ የእድገትና ብልጽግና ጉዞአችን ጮራ!” በሚል መሪ ሃሳብ የተጀመረው ጉባኤ፥ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ም/ቤት ያለፉ ወራት የእቅድ አፈጻጸም ላይ እየመከረ ነው።
ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ፍቃዱ ባስተላለፉት መልዕክት እንደ ሀገር የህዳሴ ግድብ ግንባታውን በ2017 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ ባለበት ማግስት የሚካሄድ ጉባኤ በመሆኑ ልዩ መነቃቃት የሚፈጥር ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ አሼቦ በበኩላቸው፥ ከነባሩ ክልል እስከ አዲሱ ክልል ድረስ የተከናወኑ የእቅድ አፈጻጸም አቅርበው ዝርዝር ውይይት እየተካሔደ ነው።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የአለም አቀፉን ተለዋዋጭ ሁኔታ በአግባቡ ለይቶ የሀገር ውስጥ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወልቂጤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ