በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ የሚሰጡ የማህበረሰብ ክፍል ተወካዮችን ለመምረጥ የሚያስችል የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው
በመድረኩ ላይ ወጣቶች፣ መምህራን፣ አርሶ አደሮች፣ ነጋዴዎች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ከልዩ ወረዳው የተወጣጡ 100 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው በውይይቱ በመሳተፍ ላይ የሚገኙት።
የመድረኩ ተሳታፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ከእያንዳንዱ የማህበረሰብ ክፍል አጀንዳ የሚሰጡ ሁለት ሁለት ተወካዮች ከአንዳንድ ተጠባባቂ ጋር ይመርጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉጌታ አጎን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ጅላሉ ፈድሉ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የአለም አቀፉን ተለዋዋጭ ሁኔታ በአግባቡ ለይቶ የሀገር ውስጥ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወልቂጤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ