በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ የሚሰጡ የማህበረሰብ ክፍል ተወካዮችን ለመምረጥ የሚያስችል የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው
በመድረኩ ላይ ወጣቶች፣ መምህራን፣ አርሶ አደሮች፣ ነጋዴዎች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ከልዩ ወረዳው የተወጣጡ 100 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው በውይይቱ በመሳተፍ ላይ የሚገኙት።
የመድረኩ ተሳታፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ከእያንዳንዱ የማህበረሰብ ክፍል አጀንዳ የሚሰጡ ሁለት ሁለት ተወካዮች ከአንዳንድ ተጠባባቂ ጋር ይመርጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉጌታ አጎን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ጅላሉ ፈድሉ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን ተከትሎ የምስጋናና የዕውቅና መርሃ-ግብር ተካሄደ
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ