በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጀንዳ የሚሰጡ የማህበረሰብ ክፍል ተወካዮችን ለመምረጥ የሚያስችል የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሄደ ነው
በመድረኩ ላይ ወጣቶች፣ መምህራን፣ አርሶ አደሮች፣ ነጋዴዎች፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ከልዩ ወረዳው የተወጣጡ 100 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ናቸው በውይይቱ በመሳተፍ ላይ የሚገኙት።
የመድረኩ ተሳታፊዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ከእያንዳንዱ የማህበረሰብ ክፍል አጀንዳ የሚሰጡ ሁለት ሁለት ተወካዮች ከአንዳንድ ተጠባባቂ ጋር ይመርጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሙሉጌታ አጎን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ጅላሉ ፈድሉ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ