የጋርዱላ ዞን ህዝቦች የፊላና ባህል ፌስቲቫል እንዲሁም የዘመን መለወጫ “ሀይሶት ህርባ” በዓል በዞኑ ማዕከል ጊዶሌ ከተማ በነገዉ ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል
ሀዋሳ፡ ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጋርዱላ ዞን ህዝቦች የፊላና ባህል ፌስቲቫል እንዲሁም የዘመን መለወጫ “ሀይሶት ህርባ” በዓል በዞኑ ማዕከል ጊዶሌ ከተማ በነገዉ ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታን ተከትሎ ወደ ዞን መዋቅር የተሸጋገረዉ የጋርዱላ ዞን ይፋዊ ምስረታም ይካሄዳል።
በዛሬው ዕለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ “የምሁራን አንድነትና ህብረት ለጋርዱላ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የሰላምና ልማት ሲምፖዚየም መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የአከባቢዉ ተወላጅ ምሁራን፣ የሐይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በጋርዱላ ዞን የዲራሼ፣ ኩሱሜ፣ ማሾሌና ሞስዬ አራት ብሔረሰቦችን ጨምሮ መላዉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ ይኖራል።
ዘጋቢ፡ ድልነሳዉ ታደሰ
More Stories
ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅን ምክንያት በማድረግ የይርጋጨፌ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ
ሙያዊ ስነ-ምግባር የተላበሰ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
የካፋ ዞን ጤና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት ላይ ውይይት እያካሄደ ነው