የጋርዱላ ዞን ህዝቦች የፊላና ባህል ፌስቲቫል እንዲሁም የዘመን መለወጫ “ሀይሶት ህርባ” በዓል በዞኑ ማዕከል ጊዶሌ ከተማ በነገዉ ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል
ሀዋሳ፡ ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጋርዱላ ዞን ህዝቦች የፊላና ባህል ፌስቲቫል እንዲሁም የዘመን መለወጫ “ሀይሶት ህርባ” በዓል በዞኑ ማዕከል ጊዶሌ ከተማ በነገዉ ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታን ተከትሎ ወደ ዞን መዋቅር የተሸጋገረዉ የጋርዱላ ዞን ይፋዊ ምስረታም ይካሄዳል።
በዛሬው ዕለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ “የምሁራን አንድነትና ህብረት ለጋርዱላ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የሰላምና ልማት ሲምፖዚየም መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የአከባቢዉ ተወላጅ ምሁራን፣ የሐይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በጋርዱላ ዞን የዲራሼ፣ ኩሱሜ፣ ማሾሌና ሞስዬ አራት ብሔረሰቦችን ጨምሮ መላዉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ ይኖራል።
ዘጋቢ፡ ድልነሳዉ ታደሰ

More Stories
በዶሮ እርባታ ዘርፍ በመሰማራት የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የየም ዞን ሣጃ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች ተናገሩ
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የዱራሜ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በአዲስ መልክ በዘመናዊ ዲዛይን እየተሰራ መሆኑን የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ገለፀ