የጋርዱላ ዞን ህዝቦች የፊላና ባህል ፌስቲቫል እንዲሁም የዘመን መለወጫ “ሀይሶት ህርባ” በዓል በዞኑ ማዕከል ጊዶሌ ከተማ በነገዉ ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል
ሀዋሳ፡ ጥር 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጋርዱላ ዞን ህዝቦች የፊላና ባህል ፌስቲቫል እንዲሁም የዘመን መለወጫ “ሀይሶት ህርባ” በዓል በዞኑ ማዕከል ጊዶሌ ከተማ በነገዉ ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት ይከበራል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታን ተከትሎ ወደ ዞን መዋቅር የተሸጋገረዉ የጋርዱላ ዞን ይፋዊ ምስረታም ይካሄዳል።
በዛሬው ዕለት በዓሉን ምክንያት በማድረግ “የምሁራን አንድነትና ህብረት ለጋርዱላ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የሰላምና ልማት ሲምፖዚየም መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የአከባቢዉ ተወላጅ ምሁራን፣ የሐይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በጋርዱላ ዞን የዲራሼ፣ ኩሱሜ፣ ማሾሌና ሞስዬ አራት ብሔረሰቦችን ጨምሮ መላዉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ ይኖራል።
ዘጋቢ፡ ድልነሳዉ ታደሰ

More Stories
7ኛ ዙር ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫ በመሆናቸው ለህዝብ ተጠቃሚነት ቅድሚያ ሰጥተው እየሰሩ መሆናቸው ተጠቆመ
የአለም አቀፉን ተለዋዋጭ ሁኔታ በአግባቡ ለይቶ የሀገር ውስጥ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ