እንደ ምክር ቤቱ የህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዱንጋ ናኩዋ ገለፃ በዞኑ በፍትህ ስርአቱ የሚከናወኑ የቅንጅት ስራዎች በጠንካራ ጎናቸው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።
በሳውላ ማረሚያ ተቋም አሁን ላይ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አፈፃፀማቸው መልካም ቢሆንም ሊስተካከሉ የሚገባቸው ስራዎች በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ቋሚ ኮሚቴው አስታውቋል።
በዞኑ በወንጀል አስከፊነት እንዲሁም መረጃን ወቅታዊ ከማድረግ አኳያ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ያለው ቋሚ ኮሚቴው በተለይ ለፀጥታ ችግር ሊሆኑ ይችላሉ የተባሉ ሁነቶች ላይ ዞኑ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
እንደ ጎፍ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ፍንታዬ በቋሚ ኮሚቴው የተደረጉ የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች ቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት አጋዥ መሆናቸውን ገልፀው ሊስተካከሉ ይገባል የተባሉ ስራዎች በትኩረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
ቅንጅታዊ ስራ ሊጠናከር ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ይህንም ለማገዝ የዞኑ አስተዳደር ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን ተከትሎ የምስጋናና የዕውቅና መርሃ-ግብር ተካሄደ
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ