እንደ ምክር ቤቱ የህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዱንጋ ናኩዋ ገለፃ በዞኑ በፍትህ ስርአቱ የሚከናወኑ የቅንጅት ስራዎች በጠንካራ ጎናቸው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።
በሳውላ ማረሚያ ተቋም አሁን ላይ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አፈፃፀማቸው መልካም ቢሆንም ሊስተካከሉ የሚገባቸው ስራዎች በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ቋሚ ኮሚቴው አስታውቋል።
በዞኑ በወንጀል አስከፊነት እንዲሁም መረጃን ወቅታዊ ከማድረግ አኳያ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ያለው ቋሚ ኮሚቴው በተለይ ለፀጥታ ችግር ሊሆኑ ይችላሉ የተባሉ ሁነቶች ላይ ዞኑ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
እንደ ጎፍ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ፍንታዬ በቋሚ ኮሚቴው የተደረጉ የክትትልና የቁጥጥር ስራዎች ቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት አጋዥ መሆናቸውን ገልፀው ሊስተካከሉ ይገባል የተባሉ ስራዎች በትኩረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።
ቅንጅታዊ ስራ ሊጠናከር ይገባል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ይህንም ለማገዝ የዞኑ አስተዳደር ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ