በወላይታ ዞን ዳሞት ወይዴ ወረዳ የበዴሣ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የወላድ እናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገለፀ
ሀዋሳ፡ ጥር 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወላይታ ዞን ዳሞት ወይዴ ወረዳ የበዴሣ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የወላድ እናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡
ሆስፒታሉ በዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎች የተካነ መሆኑ የተገልጋይ ዕርካታን ያሳደገ ስለመሆኑም ተመላክቷል፡፡
ከአጎራባች ወረዳዎች የሚመጡ ታካሚዎች ጭምር ተገቢውን አገልግሎት አግኝተው እንደሚመለሱ ከሆስፒታሉ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በበዴሣ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሳምሶን ሚልክያስ እንደተናገሩት፣ ምንም እንኳን ሆስፒታሉ በቅርብ ጊዜ የተቋቋመ ቢሆንም በዞኑ ውስጥ ከሚገኙ ነባር የሕክምና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ያልተናነሱ የተለያዩ የሕክምና አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል።
መለስተኛ ቀዶ ሕክምናን ጨምሮ በርካታ የሕክምና አገልግሎቶችም በበዴሣ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እየተሰጡ እንደሚገኙ አቶ ሳምሶን ገልፃዋል።
የነገ አገር ተረካቢ ዜጎችን ከማፍራት አኳያ የጨቅላ ሕፃናትን ሞት መቀነስ እንዲሁም እናቶች በጤና ተቋማት እንዲወልዱ ግንዛቤ ከማስጨበጥ አንስቶ መጠነ-ሰፊ ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ በሆስፒታሉ የሜዲካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ብሩክ ኢያሱ ተናገረዋል።
የእናቶችና የሕፃናት ሕክምና ክፍል አስተባባሪ የሆኑት አቶ ክፍሌ ለማ እንደገለጹት፣ ለእናቶችና ሕፃናት የሚሰጠው የሕክምና አገልግሎት የእናቶችና ሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የታቀደ ነው።
በዚህም በተለያዩ ዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎች የታገዘ አገልገሎት ስለሚሰጥ በርካታ ተገልጋዮች ወደ ሆስፒታሉ ይመጣሉ።
በሆስፒታሉ የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት ከመጡ ወላድ እናቶች መካከል ወይዘሮ መቅደስ አልታዬ እና ወይዘሮ መሠረት ኤልያስ በተደረገላቸው የሕክምና ዕርዳታ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ሌሎች እናቶችም በጤና ተቋማት የመውለድ ልምድ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም እናቶቹ በጋራ በሰጡት አስተያየት አረጋግጠዋል።
ዘጋቢ : ፍቃዱ ማቴዎስ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የአለም አቀፉን ተለዋዋጭ ሁኔታ በአግባቡ ለይቶ የሀገር ውስጥ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወልቂጤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ