ሁሉም በተሰማራበት የሙያ መስክ ውጤታማ ለመሆን በመትጋት ለጋራ ለውጥ ሊረባረብ እንደሚገባ የጌዴኦ አባ ገዳ ቢፎም ዋቆ ገለፁ
ሀዋሳ፡ ጥር 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ)ሁሉም በተሰማራበት የሙያ መስክ ውጤታማ ለመሆን በመትጋት ለጋራ ለውጥ ሊረባረብ እንደሚገባ የጌዴኦ አባ ገዳ ቢፎም ዋቆ ገለፁ፡፡
ይህም የተባለው የብሔሩ ዘመን መለወጫና የምስጋና ዳራሮ በዓል በጌዴኦ ዞን ጨለለቅቱ ከተማ አስተዳደር በተከበረበት ነው፡፡
የጌዴኦ ብሔር አባገዳ ቢፎሚ ዋቆ ዳራሮ የአንድነት የወንድማማችነትና የምስጋና በዓል መሆኑን ጠቁመው ትውልዱ በየተሰማራበት የሙያና የሥራ ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን መትጋት እንዳለበት ገልፀዋል፡፡
አከባቢው ያለው መሬት ጠባብ በመሆኑ ትውልዱ በትምህርት ላይ እንዲያተኩርና የሥራ ባህሉን እንዲያጎለብት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት አባገዳ ቢፎሚ ፈጣሪ የአከባቢው ሠላም ጠብቆ እንዲያቆይ ምርታማነት እንዲጨምር ፈጣሪ የተሻለ ዝናብ ለአከባቢው እንዲሰጥ ፈጣሪን ተማፅኗል፡፡
በዞኑ የጨጨለቅቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተስፋዬ ፈይሳ ለብሔሩ ዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል ለሆነው ዳራሮ በዓል በዞኑ ለሚገኙና አጎራባች አከባቢዎች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፏል፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ አሁን ያለውን የዞኑን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ መንግስት የያዛቸውን ዕቅዶች ከዳር ለማድረስና የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በሚደረገው ጥረት ሁሉም በጋራ እንዲረባረብ አሳስቧል፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአለም አቀፉን ተለዋዋጭ ሁኔታ በአግባቡ ለይቶ የሀገር ውስጥ ተጋላጭነትን መቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በትኩረት በመስራት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ገለፁ
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወልቂጤ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ