ሁሉም በተሰማራበት የሙያ መስክ ውጤታማ ለመሆን በመትጋት ለጋራ ለውጥ ሊረባረብ እንደሚገባ የጌዴኦ አባ ገዳ ቢፎም ዋቆ ገለፁ
ሀዋሳ፡ ጥር 14/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ)ሁሉም በተሰማራበት የሙያ መስክ ውጤታማ ለመሆን በመትጋት ለጋራ ለውጥ ሊረባረብ እንደሚገባ የጌዴኦ አባ ገዳ ቢፎም ዋቆ ገለፁ፡፡
ይህም የተባለው የብሔሩ ዘመን መለወጫና የምስጋና ዳራሮ በዓል በጌዴኦ ዞን ጨለለቅቱ ከተማ አስተዳደር በተከበረበት ነው፡፡
የጌዴኦ ብሔር አባገዳ ቢፎሚ ዋቆ ዳራሮ የአንድነት የወንድማማችነትና የምስጋና በዓል መሆኑን ጠቁመው ትውልዱ በየተሰማራበት የሙያና የሥራ ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን መትጋት እንዳለበት ገልፀዋል፡፡
አከባቢው ያለው መሬት ጠባብ በመሆኑ ትውልዱ በትምህርት ላይ እንዲያተኩርና የሥራ ባህሉን እንዲያጎለብት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት አባገዳ ቢፎሚ ፈጣሪ የአከባቢው ሠላም ጠብቆ እንዲያቆይ ምርታማነት እንዲጨምር ፈጣሪ የተሻለ ዝናብ ለአከባቢው እንዲሰጥ ፈጣሪን ተማፅኗል፡፡
በዞኑ የጨጨለቅቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተስፋዬ ፈይሳ ለብሔሩ ዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል ለሆነው ዳራሮ በዓል በዞኑ ለሚገኙና አጎራባች አከባቢዎች ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፏል፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ አሁን ያለውን የዞኑን ሰላም በዘላቂነት በመጠበቅ መንግስት የያዛቸውን ዕቅዶች ከዳር ለማድረስና የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በሚደረገው ጥረት ሁሉም በጋራ እንዲረባረብ አሳስቧል፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ