ሀዋሳ፡ ጥር 12/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአርብቶ አደር ማህብረሰብ ክፍሎችን ሁሉ አቀፍ ለውጥ ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ታረቀኝ ሀብቴ ገለፁ።
የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ እንደገለፁት መንግሥት የአርብቶ አደር ማህብረሰብን ኑሮ ለማሻሻል ልዩ ፖሊሲ ቀርፆ እየሠራ ይገኛል።
ለአርብቶ አደሩ ለውጥ የማይሆኑ ኋላ ቀር እና ጎታች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት በቀጠናው የተሻለ ሠላም እንዲሰፍን እና ለውጥ እንዲመዘገብ ከ58 ሺህ በላይ ለሆኑ አርብቶ አደሮች ግንዛቤ መፈጠሩን አቶ ማዕከል ገልፀዋል።
የአርብቶ አደር አካባቢ በከፍተኛ ሁኔታ ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት ያለውና በዚህ ልክ የውሃ አማራጮች መኖሩን አቶ ማዕከል ጠቅሰው ይህንን ፀጋ ወደ ተግባር በመቀየር ለተሻለ ለውጥ እየተሠራ ስለመሆኑም ተናግረዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ታረቀኝ ሀብቴ እንዳሉት በአርብቶ አደር አካባቢ ዘላቂ ልማት እንዲረጋገጥ በክልሉ እየተሠራ ይገኛል።
ይህ እንዲሳካ በየደረጃው የሚገኙ አካላት በሙሉ የድርሻቸውን እንዲወጡ የቢሮ ሀላፊው ጥሪ አቅርበዋል።
በቱሪዝም ሀብትና በእምቅ የተፈጥሮ ማዕድናት የበለፀገው አርብቶ አደር አካባቢ ቀጣይነት ባለው መልኩ ለውጥ እንዲያስመዘግብ ቢሮው ከልማት አጋር አካላትና በአካባቢው በኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሠማሩ እና ከሌሎች ጋር በቅንጅት እየሠራ ስለመሆኑም አስረድተዋል አቶ ታረቀኝ።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ ምርት እየለማ መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው
የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመመለስ በኩል ከመንግስት ጥረት ባለፈ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና የጎላ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ተናገሩ