ሀዋሳ፡ ጥር 12/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኦሞ ዞን 10ኛው አርብቶ አደሮች ቀን በዓል “አርብቶ አደርነት የምስራቅ አፍርካ ህብረ ቀለም” በሚል መሪ ቃል በዲመካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ ወ/ሮ ወላይቴ ቢቶ፣ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ አቶ ዳርጌ ዳሼን፣ የአካባቢው የህዝቦች ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች፣ የበዓሉ ባለቤት የሆኑ አርብቶ አደሮች፣ ከአጎራባች ኬንያ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሌሎችም ተገኝተዋል።
በመድረኩ በቀጣይ በአርብቶ አደሮች አካባቢ ሰፋፊ ልማቶችን ይበልጥ ለማረጋገጥ ልዩ ውሳኔ እንደሚተላለፍና በዘርፉ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ዕውቅና እንደሚሰጣቸውም ከወጣው መርሐ ግብር ለመረዳት ተችሏል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በስልጤ ዞን የሚገኘው ሃይረንዚ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2017 የትምህርት ዘመን በሃገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ላይ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እና ውጤቱ እንዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላደረጉ መምህራን የማትጊያና የእውቅና ፕሮግራም ተካሄደ
የዋካ ቅርንጫፍ ጣቢያ ወቅታዊና ጥራት ያለውን መረጃ ተደራሽ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በላቀ ደረጃ እንዲወጣ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ