ሀዋሳ፡ ጥር 12/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኦሞ ዞን 10ኛው አርብቶ አደሮች ቀን በዓል “አርብቶ አደርነት የምስራቅ አፍርካ ህብረ ቀለም” በሚል መሪ ቃል በዲመካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ ወ/ሮ ወላይቴ ቢቶ፣ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ አቶ ዳርጌ ዳሼን፣ የአካባቢው የህዝቦች ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች፣ የበዓሉ ባለቤት የሆኑ አርብቶ አደሮች፣ ከአጎራባች ኬንያ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሌሎችም ተገኝተዋል።
በመድረኩ በቀጣይ በአርብቶ አደሮች አካባቢ ሰፋፊ ልማቶችን ይበልጥ ለማረጋገጥ ልዩ ውሳኔ እንደሚተላለፍና በዘርፉ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ዕውቅና እንደሚሰጣቸውም ከወጣው መርሐ ግብር ለመረዳት ተችሏል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ