ሀዋሳ፡ ጥር 12/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኦሞ ዞን 10ኛው አርብቶ አደሮች ቀን በዓል “አርብቶ አደርነት የምስራቅ አፍርካ ህብረ ቀለም” በሚል መሪ ቃል በዲመካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ ወ/ሮ ወላይቴ ቢቶ፣ የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ አቶ ዳርጌ ዳሼን፣ የአካባቢው የህዝቦች ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ የክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች፣ የበዓሉ ባለቤት የሆኑ አርብቶ አደሮች፣ ከአጎራባች ኬንያ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሌሎችም ተገኝተዋል።
በመድረኩ በቀጣይ በአርብቶ አደሮች አካባቢ ሰፋፊ ልማቶችን ይበልጥ ለማረጋገጥ ልዩ ውሳኔ እንደሚተላለፍና በዘርፉ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ዕውቅና እንደሚሰጣቸውም ከወጣው መርሐ ግብር ለመረዳት ተችሏል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮረሪማ ምርት እየለማ መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን ከ12 ሺህ በላይ ተማሪዎች ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና እየተሰጠ ነው
የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመመለስ በኩል ከመንግስት ጥረት ባለፈ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሚና የጎላ መሆኑን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ ተናገሩ