የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የህዝባቸውን የልማት ጥያቄ ለመመለስ እየተቸገሩ ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ሀዋሳ፡ ጥር 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የህዝባቸውን የልማት ጥያቄ ለመመለስና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ከፍተኛ ፈተና እንደሆነባቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የባህር በር የሌላት ኢትዮጵያም ችግሩን ለመፍታት በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ መሰረት ጥረት እያደረገች እንደሆነ ማስረዳታቸውን በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የልዑካን ቡድናቸው በዑጋንዳ ካምፓላ በተካሄደው የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ ርዕሳነ ብሔር እና ርዕሳነ መንግሥታት 19ኛው ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል።

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ