በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶችን ማልማትና መጠበቅ እንደሚያስፈልግ የአሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ገለፀ
ሀዋሳ፡ ጥር 02/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶችን ማልማትና መጠበቅ እንደሚያስፈልግ የአሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ገልጿል፡፡
መምሪያው የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወራት አፈፃፀም ግምገማ እና ቀጣይ የቀሪ ስድስት ወር ዕቅድ ዙሪያ የሚመክር የባለድርሻ አካላት እና የህዝብ ክንፍ ምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የአሪ ዞን ምክትል አስተዳደርና ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ታፈሰ ተስፋዬ እንደገለፁት፤ በየአካባቢው በርካታ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህቦች በመኖራቸው ይህንን ማልማትና መጠበቅ ከሁሉም ይጠበቃል።
መመሪያው በዞኑ ስር ያሉ እምቅ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማስተዋወቅ እየሠራ ስለመሆኑ የገለፁት የአሪ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊ አቶ ኤልያስ ቃሾ ናቸው።
መድረኩ በመምሪያ በኩል የተከናወኑ ተግባራትን እያደመጠ የሚገኝ ሲሆን ሰፊ ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ