የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፤ ጥር 2/2016 ዓ.ም. (ደሬቴድ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ለመንግስታዊ ስራ አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል፡፡
ሚኒስትሩ ወደ አርባምጭ ከተማ ሲገቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ለሚኒስትሩ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።
ሚኒስትሩ በአርባምንጭ ቆይታቸው በኢትዮጵያ ታምርት መርሃ ግብር የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ተኪ ምርት ስትራቴጂ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ይሳተፋሉ።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ