የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፤ ጥር 2/2016 ዓ.ም. (ደሬቴድ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ለመንግስታዊ ስራ አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል፡፡
ሚኒስትሩ ወደ አርባምጭ ከተማ ሲገቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ለሚኒስትሩ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።
ሚኒስትሩ በአርባምንጭ ቆይታቸው በኢትዮጵያ ታምርት መርሃ ግብር የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ተኪ ምርት ስትራቴጂ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ይሳተፋሉ።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ