የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል አርባምንጭ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፤ ጥር 2/2016 ዓ.ም. (ደሬቴድ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ለመንግስታዊ ስራ አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል፡፡
ሚኒስትሩ ወደ አርባምጭ ከተማ ሲገቡ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ለሚኒስትሩ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።
ሚኒስትሩ በአርባምንጭ ቆይታቸው በኢትዮጵያ ታምርት መርሃ ግብር የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ተኪ ምርት ስትራቴጂ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ይሳተፋሉ።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ
ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎችን በመስራታቸው ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ማግኘታቸውን የአርባምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኮሌጅ ተማሪዎችና መምህራን ገለፁ