በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ የሚገኘው የጋልማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ተመረቀ

በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ የሚገኘው የጋልማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ተመረቀ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ኮሌጁን በይፋ መርቀው ሲከፍቱ እንዳሉት ኮሌጁ በብርቱ ክትትል በ8 ወር ውስጥ ተጠናቋል ብለዋል::

ኮሌጁ አምራች ዜጎችን እንዲፈጥር በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የመንግስት እጅን የማይጠብቁ ለሌሎችም የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ወጣቶች መፍጠር ይኖርባቸዋል ብለዋል።

ህንፃው ፍሬያማ የሚሆነዉ ተማሪዎች በፍላጎታቸው ተመዝግበው እንዲማሩ በማድረግ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ መንግስትም ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ብለዋል።

ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ