በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ የሚገኘው የጋልማ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ተመረቀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ኮሌጁን በይፋ መርቀው ሲከፍቱ እንዳሉት ኮሌጁ በብርቱ ክትትል በ8 ወር ውስጥ ተጠናቋል ብለዋል::
ኮሌጁ አምራች ዜጎችን እንዲፈጥር በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል። የመንግስት እጅን የማይጠብቁ ለሌሎችም የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ወጣቶች መፍጠር ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ህንፃው ፍሬያማ የሚሆነዉ ተማሪዎች በፍላጎታቸው ተመዝግበው እንዲማሩ በማድረግ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ መንግስትም ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ባዬ በልስቲ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ