“ከእዳ ወደ ምንዳ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የመንግስት አመራሮች ስልጠና በአርባምንጭ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል
የደቡብ ኢትዮጵያዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ እንደተናገሩት የሀገሪቱን ቀጣይ የብልፅግና ጉዞን ማሳካት የሚችሉ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ያስፈልጋሉ።
አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥትም የክልሉን ህዝቦች የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን ማመዛዘንና በፍጥነት ቀድሞ መገኘት የሚችል አመራር በሚሻበት ወቅት ይህ ስልጠና መዘጋጀቱ ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።
በአርባምንጭ ከተማ የሚሰጠውን የአመራሮች ስልጠና ለመውሰድ የመጡ አንግዶች በጋሞ አባቶች እና በህዝቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
ዘጋቢ: በኃይሉ ሙሉጌታ- ከአርባምንጭ

More Stories
ለትምህርት ሥራ ስኬታማነት ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነትና በጋራ መስራት እንዳለባቸው ተገለፀ
በበጀት አመቱ በ71 ሺህ 219 መዛግብት ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ማህበረሰብ ባህላዊ እሴቶች ሳይበረዙ ለትውልድ ለማስተላለፍ የኪነ ጥበብ ዘርፉን በማጠናከር ላይ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ