የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ይፋዊ ምስረታ ህደር 13 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚካሄድ የክልሉ ርዕሰ መስተደድር አቶ ጥላሁን ከበደ አስታወቁ
በዝግጅቱ ዙሪያ በአዲስ አበባ ከሚገኙ የክልሉ ተወላጅ አመራሮች ጋር በአዲስ አበባ ውይይት እየተደረገ ነው።
በአዲስ አበባ እና በፌዴራል ተቋማት ለሚገኙ የክልሉ ተወላጅ አመራሮች የእስካሁኑን ቅድመ ዝግጅቶችና የይፋዊ ምስረታ ዓላማዎች ላይ ገለጻ አድርገዋል።
በህዳር 13ቱ ይፋዊ ምስረታ ላይ ከቀበሌ ጀምሮ ያሉ የክልሉ ተወላጆች ተሳትፎና ይሁንታ የሚያደርጉበት እንደሚሆን ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።
ህደር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የክልሉ ይፋዊ ምስረታ የተለያዩ ክልሎችና ተቋማት ድጋፍና አጋርነት የሚገልጹበት እንደሚሆን አቶ ጥላሁን አስታውቀዋል።
የቅድመ ዝግጅት ሥራዎቹ በአብይና ንኡሳን ኮሚቴዎች እየተሰሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡
ህደር 13 ቀን 2016 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚካሄደው በዚሁ ይፋዊ ምስረታ የአዲስ አበባ እና የፌዴራል ተቋማት አመራሮች ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 12 ዞኖችን ይዞ የተዋቀረ እና በ6 ማዕላት የተደራጀ ክልል መሆኑ ይታወቃል።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ በመማር ማስተማር ዘርፍ እየተመዘገቡ የሚገኙ ለወጦች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 5.5 ቢሊየን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ወደስራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ
በዳዉሮ ዞን እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች ለህዝቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ እያስገኙ መሆናቸዉ ትኩረት ሊደረግባቸው እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ