ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል መረቁ
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ3 ዓመት በፊት እንዲቋቋም አቅጣጫ ባስቀመጡት መሰረት አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ዛሬ ረፋድ ላይ መመረቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ማዕከሉ በተፈጥሮ እና በአደጋ ምክንያት የአካል ጉዳተኛ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገር ውስጥ አጋዥ ቁሶችን ለማምረት እና ለማቅረብ የተቋቋመ ማዕከል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል አጋዥ ቴክኖሎጂዎችን ለማምረት፣ ለማደስ እና ለማቅረብ የተቋቋመ ሲሆን ተደራሽ፣ ጥራት ያለው እና ደንበኛ ተኮር የሰው ሰራሽ እና የአካል ድጋፎች አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ