ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል መረቁ
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ3 ዓመት በፊት እንዲቋቋም አቅጣጫ ባስቀመጡት መሰረት አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ዛሬ ረፋድ ላይ መመረቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ማዕከሉ በተፈጥሮ እና በአደጋ ምክንያት የአካል ጉዳተኛ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገር ውስጥ አጋዥ ቁሶችን ለማምረት እና ለማቅረብ የተቋቋመ ማዕከል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል አጋዥ ቴክኖሎጂዎችን ለማምረት፣ ለማደስ እና ለማቅረብ የተቋቋመ ሲሆን ተደራሽ፣ ጥራት ያለው እና ደንበኛ ተኮር የሰው ሰራሽ እና የአካል ድጋፎች አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።
More Stories
ፓርቲዉ ባለፉት 3 ዓመታት የብዝሃ ኢኮኖሚ መሪህ በመከተል እንደሀገር ዉጤታማ ተግባራትን ፈጽሟል-ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ
በክልሉ በምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ ኮካ ቀበሌ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የእንስሳት ክትባት እየተሰጠ ነው
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተራና የጥምቀት በዓላት በሰላማዊ መንገድ ተከብረው እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ