ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል መረቁ
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ3 ዓመት በፊት እንዲቋቋም አቅጣጫ ባስቀመጡት መሰረት አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ዛሬ ረፋድ ላይ መመረቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ማዕከሉ በተፈጥሮ እና በአደጋ ምክንያት የአካል ጉዳተኛ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገር ውስጥ አጋዥ ቁሶችን ለማምረት እና ለማቅረብ የተቋቋመ ማዕከል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል አጋዥ ቴክኖሎጂዎችን ለማምረት፣ ለማደስ እና ለማቅረብ የተቋቋመ ሲሆን ተደራሽ፣ ጥራት ያለው እና ደንበኛ ተኮር የሰው ሰራሽ እና የአካል ድጋፎች አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።
More Stories
የሴቶች የልማት ህብረትን በማጠናከር የሴቶችን ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ