ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል መረቁ
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ3 ዓመት በፊት እንዲቋቋም አቅጣጫ ባስቀመጡት መሰረት አዲስ የተቋቋመውን የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ዛሬ ረፋድ ላይ መመረቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ማዕከሉ በተፈጥሮ እና በአደጋ ምክንያት የአካል ጉዳተኛ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገር ውስጥ አጋዥ ቁሶችን ለማምረት እና ለማቅረብ የተቋቋመ ማዕከል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ አካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል አጋዥ ቴክኖሎጂዎችን ለማምረት፣ ለማደስ እና ለማቅረብ የተቋቋመ ሲሆን ተደራሽ፣ ጥራት ያለው እና ደንበኛ ተኮር የሰው ሰራሽ እና የአካል ድጋፎች አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ የሚሰጥ መሆኑም ተገልጿል።
More Stories
የህብረተሰቡን ጤና ለማጎልበት የዘርፉን ተግባራት በተገቢው ለማሳካት ከምንጊዜውም በተሻለ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ