የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 15/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዞኑ ፋይናንስ አግልግሎት አሰጣጥ ላይ እየገጠሙ ያሉ ችግሮች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ የጋራ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በዲላ ከተማ ተካሂዷል።
ውይይቱን የመሩት የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማ ጤካሞ በ2016 አጠቃላይ በጀትና በፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ለባለድርሻ አካላት አብራርተዋል።
አምና በተሰበበው ገቢ ላይ ከ8 መቶ ሚሊየን ብር በላይ መጨመሩን የገለጹት ኃላፊ አሁን ላይ እየገጠሙን ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ሁሉም መዋቅር ገቢ አሟጦ መሰብሰብ አለበት ነው ያሉት።
አሰተያየታቸውን የሰጡት ተሳታፊዎችም እንደሀገር የጥሬ ገንዘብ እጥረት መኖሩን አንስተው እነዚህ ችግሮችን ለመቋቋም ገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ሁሉም የባለድርሻ አካላት መፍትሔ ነው ያሏቸውን ሀሳቦች እያነሱ በጥልቀት ተወያይተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከፍስሃገነት ጣቢያችን
More Stories
የፍትህ ተቋማት ተገልጋዩን ህብረተሰብ በሚመጥን መልኩ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ
በተገልጋይ እርካታና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ
የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑ ተጠቆመ