የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 15/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዞኑ ፋይናንስ አግልግሎት አሰጣጥ ላይ እየገጠሙ ያሉ ችግሮች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ የጋራ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በዲላ ከተማ ተካሂዷል።
ውይይቱን የመሩት የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማ ጤካሞ በ2016 አጠቃላይ በጀትና በፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ለባለድርሻ አካላት አብራርተዋል።
አምና በተሰበበው ገቢ ላይ ከ8 መቶ ሚሊየን ብር በላይ መጨመሩን የገለጹት ኃላፊ አሁን ላይ እየገጠሙን ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ሁሉም መዋቅር ገቢ አሟጦ መሰብሰብ አለበት ነው ያሉት።
አሰተያየታቸውን የሰጡት ተሳታፊዎችም እንደሀገር የጥሬ ገንዘብ እጥረት መኖሩን አንስተው እነዚህ ችግሮችን ለመቋቋም ገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ሁሉም የባለድርሻ አካላት መፍትሔ ነው ያሏቸውን ሀሳቦች እያነሱ በጥልቀት ተወያይተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከፍስሃገነት ጣቢያችን

More Stories
የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለሕብረተሰቡ ግንዛቤን ከመፍጠር ጀምሮ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል – የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽህፈት ቤት
በከምባታ ዞን የሺንሽቾ ከተማ የመሠረተ ልማት ተግባራት በማጠናከር የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ86 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ