የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 15/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዞኑ ፋይናንስ አግልግሎት አሰጣጥ ላይ እየገጠሙ ያሉ ችግሮች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ የጋራ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በዲላ ከተማ ተካሂዷል።
ውይይቱን የመሩት የጌዴኦ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማ ጤካሞ በ2016 አጠቃላይ በጀትና በፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ለባለድርሻ አካላት አብራርተዋል።
አምና በተሰበበው ገቢ ላይ ከ8 መቶ ሚሊየን ብር በላይ መጨመሩን የገለጹት ኃላፊ አሁን ላይ እየገጠሙን ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ሁሉም መዋቅር ገቢ አሟጦ መሰብሰብ አለበት ነው ያሉት።
አሰተያየታቸውን የሰጡት ተሳታፊዎችም እንደሀገር የጥሬ ገንዘብ እጥረት መኖሩን አንስተው እነዚህ ችግሮችን ለመቋቋም ገቢ ሰብሳቢ ተቋማት ጠንክረው መሥራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ሁሉም የባለድርሻ አካላት መፍትሔ ነው ያሏቸውን ሀሳቦች እያነሱ በጥልቀት ተወያይተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከፍስሃገነት ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በጋሞ ዞን በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የወረዳውን ዕድገት ለማፋጠን የተጀመሩ የመሰረተ ልማት ተቋማት ሊፋጠኑ ይገባል
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በወ/ሮ አዱኛ አዛዥ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ