የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት በትኩረት ይሰራል – የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ
ሀዋሳ፡ መስከረም 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት በትኩረት እንደሚሠራ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው በአርባ ምንጭ ማዕከል በይፋ ሥራ መጀመሩን አስታውቋል።
የቢሮው ሀላፊ አቶ ገለቦ ጎልቶሞ የቢሮው ሠራተኞች መደበኛ ሥራቸውን ከሌላው ጊዜ በላቀ ደረጃ እዲወጡ አሳስበዋል።
የቢሮው ምክትል ሐላፊ እና የሬጉሌሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍቅርተ አብርሐም በበኩላቸው ባለሙያዎች ባለጉዳዮችን በቅንነት እና በታማኝነት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ