የፌዴሬሽን ምክር ቤት የቀረቡለትን እቅዶች መርምሮ አጸደቀ
የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት እያካሄደ ባላው 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 3ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 1ኛ መደበኛ ጉባዔ የቀረቡለትን እቅዶች መርምሮ አጽድቋል፡፡
የፌዴሬሽን ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባዔውም የሕገ-መንግሥት ትርጉምና ውሳኔ አፈጻፀም ክትትል ቋሚ ኮሚቴ፣ የመንግስታት ግንኙነት የዲሞክራሲ አንድነትና የሕገ-መንግሥት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ፣ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ፣ የማንነት፣ የአስተዳደር ወሰንና የሰላም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴና የሕገ መንግሥትና ፌዴራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ያቀረቡት የ2016 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ተወያይቶ አጽድቋል፡፡
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት የቀረቡላቸውን እቅዶች ካደመጡ በኋላ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የየቋሚ ኮሚቴዎቹ አመራሮችም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር እና ሌሎች የሥራ ሀላፊዎች በጉባዔው መገኘታቸውንም የፌዴሬሽን ምክር ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
የህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ትላንት መካሄዱ ይታወቃል።

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን ተከትሎ የምስጋናና የዕውቅና መርሃ-ግብር ተካሄደ
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ