ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! – አቶ አለማየሁ ባውዲ
ሀዋሳ፡ መስከረም 16/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡
የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ እና የመከባበር እሴቶቻችን ማሳያ ለሆነው የመስቀል በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል፡፡
የመስቀል በዓል በመላ ሀገሪቱ የሚከበር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በህዝቦች መካከል የአብሮነት የመኖር እሴቶችን የሚያጎለብት እንዲሁም የአንድነትና የመቻቻል መንፈስን የሚያጠናክር ነው።
በዓሉ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥና አንድነት መጽናት ከመቼውም ጊዜ በላይ የምንተጋበትና ትስስራችንን የበለጠ የምናፀናበት በዓል እንዲሆንም መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መልካም የመስቀል በዓል!

More Stories
በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት መስጠትና ተግቶ በመስራት ከድህነት መውጣት ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
ኢትዮጵያን ለዘመናት ከቆየችበት ቁስል ለማላቀቅ ባለፉት የለውጥ አመታት በርካታ ፖለቲካዊ ተግባራት ማከናወኑን መቻሉ ተገለጸ
ችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎችን በመስራታቸው ዘርፈ ብዙ ጠቄሜታ ማግኘታቸውን የአርባምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኮሌጅ ተማሪዎችና መምህራን ገለፁ