ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! – አቶ አለማየሁ ባውዲ
ሀዋሳ፡ መስከረም 16/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡
የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ እና የመከባበር እሴቶቻችን ማሳያ ለሆነው የመስቀል በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል፡፡
የመስቀል በዓል በመላ ሀገሪቱ የሚከበር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በህዝቦች መካከል የአብሮነት የመኖር እሴቶችን የሚያጎለብት እንዲሁም የአንድነትና የመቻቻል መንፈስን የሚያጠናክር ነው።
በዓሉ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥና አንድነት መጽናት ከመቼውም ጊዜ በላይ የምንተጋበትና ትስስራችንን የበለጠ የምናፀናበት በዓል እንዲሆንም መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መልካም የመስቀል በዓል!

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ