ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! – አቶ አለማየሁ ባውዲ

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! – አቶ አለማየሁ ባውዲ

ሀዋሳ፡ መስከረም 16/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡

የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ እና የመከባበር እሴቶቻችን ማሳያ ለሆነው የመስቀል በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል፡፡

የመስቀል በዓል በመላ ሀገሪቱ የሚከበር ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በህዝቦች መካከል የአብሮነት የመኖር እሴቶችን የሚያጎለብት እንዲሁም የአንድነትና የመቻቻል መንፈስን የሚያጠናክር ነው።

በዓሉ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥና አንድነት መጽናት ከመቼውም ጊዜ በላይ የምንተጋበትና ትስስራችንን የበለጠ የምናፀናበት በዓል እንዲሆንም መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

መልካም የመስቀል በዓል!