ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ለመስቀል ደመራ በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሰተላለፉ

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ለመስቀል ደመራ በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሰተላለፉ

ሀዋሳ፡ መስከረም 16/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዓሉን በፍቅርና በአብሮነት፣ በመረዳዳትና በመተጋገዝ፣ አቅመ ደካማ ወገኖቻችንንና አረጋዊያንን በመደገፍ በጎ ተግባራትን አየፈፀምን ማከበር እንደሚያስፈልግ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገልጸዋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁም ብለዋል።

መስቀል አምላክ ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅሩን የገለፀበት፤ ይቅርታንና የኃጢያት ስርየትን ለሰው ልጆች የሰጠበት መለኮታዊ አንድምታ ያለው ሲሆን በመስቀል ፍቅር፣ ሰላም፣ ይቅርታና መተሳሰብ የሚገለፅበት በመሆኑ በዓሉን ስናከብር የኢትዮጵያዊነታችን ማድመቂያ የእርስ በርስ መዋደዳችን መገለጫ መሆን ይገባል።

የመስቀልን ደመራ በዓል አከባበር ህዝብ በጋራና በአብሮነት በአንድ ቦታ በመሰባሰብ ማክበር አንዱ የኃይማኖታዊ ሥርዓቱ ሲሆን በአደባባይ ከኃይማኖታዊ ክዋኔ ባሻገር ለሀገሪቱ ትልቅ የቱሪዝም ሀብት ሆነዋል። ይህንን ዕንቁ በዓል የበዓል እሴቱ በጠበቀ መልክ በማክበርና ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ ትልቅ ቤት ሥራችን ነው ብለዋል።

ከበርካታ ሀገራት በዓሉን ለመታደምና ቱሪስቶች ወደ ሀገሪቱ ስለሚመጡ የተለመደውን ኢትዮጵያዊ ጨዋነታችንንና እንግዳ ተቀባይነታችንን ልናሳያቸው ይገባል ብለዋል።

ምንጭ፡ የሲዳማ ብ/ክ/መ/ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት