የካፈቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል ያለ ምንም የትራፊክ አደጋ እንዲጠናቀቅ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የካፋ ዞን ትራስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ አስታወቀ
ሀዋሳ፡ መስከረም 11/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የካፈቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል ያለ ምንም የትራፊክ አደጋ እንዲጠናቀቅ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የካፋ ዞን ትራስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ አስታውቋል፡፡
በዓሉን ለማክበር ለሚመጡ ሰዎች የማጓጓዣ እጥረት እንዳይኖር ዝግጅት መደረጉን መምሪያው ገልጿል፡፡
በቦንጋ ከተማ ቦንጌ ሻምበቶ በሚጓጓዙበት ወቅት በቂ የትራንስፖርት አቅርቦት እንዲኖር ከወረዳ እና ከተማ አስተዳደር አመራሮች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ነው የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ ዘመዴ አንዳርጌ የገለፁት፡፡
ከወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚነሱ የበዓሉ ተሳታፊዎች ያለ ምንም የትራንስፖርት እጥረት በዓሉን እክብረው ወደየመጡበት እንዲመለሱ ግብረ-ሃይል በማቋቋም እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ዘመዴ ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር መኖሩንም ጠቁመዋል፡፡
ከባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች እንዲሁም ከትራንስፖርት ማህበራት ጋር በመነጋገር የትራንስፖርት እጥረት እንዳይከሰት በቂ ዝግጅት የተደረገ ሲሆን ይህንን ሁሉም የሚመለከተው አካል ገቢራዊ እንዲያደርግ የመምሪያው ሃላፊ ጠይቀዋል፡፡
በየወረዳዎች የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ከትራፊክ ፖሊሲች ጋር በመናነበብ ምንም አይነት የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰትም የቅድመ ጥንቃቄ ስራ መሰራቱን ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ