በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄዷል።
ምክር ቤቱ በአሪ ዞን ዋና አስተዳደሪ በአቶ አብርሃም አታ በኩል የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬን ዕጩ አድርገው አቅርበው በምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
በተመሳሳይ ወ/ሮ አንለይ እርገጤ የጂንካ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ሆነው እንዲያገለግሉ የጂንካ ከተማ ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬ አቅርበው በምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
በተጨማሪ ከንቲባው አቶ ማንጎ ከበደን በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪና ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የሪዮተዓለም ዘርፍ ሀላፊ ሆነው እንዲያገለግሉ ቀርቦ በምክር ቤቱ ሙሉ ይሁንታን አግኝቷል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ባደረጉት ንግግር ከተማው የሁሉም ኢትዮጵያን በመሆኑ በጋራ አንድነትና ለለውጥ ተግተን ልንሠራ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ብዙ መልማትና መጠቀም የሚገባን የኢኮኖሚ አውታሮች በመኖራቸው በሰከነ መልኩ አንድነታችንን አጠናክረን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሠራለን ሲሉም አቶ አብርሃም አታ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ የተሾሙት የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬ በበኩላቸው የህዝቦች አንድነትና ሠላም ተረጋግጦ የተሻለ ልማትና ዕድገት በከተማው እንዲመዘገብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ምክር ቤቱም በቀረበው ሹመት አጀንዳ ዙሪያ በመምከር አስቸኳይ ጉባኤውን አጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የመምህርነት ሙያ ትውልድን የመቅረፅና ሀገርን የማነፅ ታላቅ የስልጣኔና ማህበራዊ የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ ተመራቂዎች ራሳቸውን ለማብቃት መትጋት አለባቸው – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተሻሻለ የስልጠና ጥራት፣ በተጠናከረ የኢንዱስትሪ ትስስርና ተፈላጊ ሙያተኞችን በማፍራት በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ313 ሺህ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰራጭቷል – የክልሉ ግብርና ቢሮ