በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄዷል።
ምክር ቤቱ በአሪ ዞን ዋና አስተዳደሪ በአቶ አብርሃም አታ በኩል የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬን ዕጩ አድርገው አቅርበው በምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
በተመሳሳይ ወ/ሮ አንለይ እርገጤ የጂንካ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ሆነው እንዲያገለግሉ የጂንካ ከተማ ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬ አቅርበው በምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ፀድቋል።
በተጨማሪ ከንቲባው አቶ ማንጎ ከበደን በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪና ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የሪዮተዓለም ዘርፍ ሀላፊ ሆነው እንዲያገለግሉ ቀርቦ በምክር ቤቱ ሙሉ ይሁንታን አግኝቷል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ባደረጉት ንግግር ከተማው የሁሉም ኢትዮጵያን በመሆኑ በጋራ አንድነትና ለለውጥ ተግተን ልንሠራ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ብዙ መልማትና መጠቀም የሚገባን የኢኮኖሚ አውታሮች በመኖራቸው በሰከነ መልኩ አንድነታችንን አጠናክረን እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሠራለን ሲሉም አቶ አብርሃም አታ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ የተሾሙት የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሬ በበኩላቸው የህዝቦች አንድነትና ሠላም ተረጋግጦ የተሻለ ልማትና ዕድገት በከተማው እንዲመዘገብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ምክር ቤቱም በቀረበው ሹመት አጀንዳ ዙሪያ በመምከር አስቸኳይ ጉባኤውን አጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ