ተላለፊና ድንገተኛ ወረርሽኝ በሽታዎችን ለመግታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ምክክር በጂንካ ከተማ ተካሔደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ድንገተኛ አደጋዎች ኦፕሬሽን ማዕከል ተላለፊና ድንገተኛ ወረርሽኝ በሽታዎች ዙሪያ የጋራ ምክክር በጂንካ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በጂንካ ከተማ ከተደራጁ የማህበራዊ ክላስተር ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ አንዱ ሲሆን ተቋማቱ ወደ ሥራ መግባታቸውን ተከትሎ፥ የድንገተኛ አደጋዎች ኦፕሬሽን ክላስተሩ ከተደራጀ በኋላ የመጀመሪያ የሆነውን ውይይት እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የልማት አጋር ድርጅቶች፣ የማዕከሉ አመራሮች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ታዬን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው በ36 ሳምንታት አፈፃፀም ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ወባ፣ ኮሌራ የምግብ እጥረት እና በሌሎችም በወረርሽኝ መልክ ሊገለፁ በሚችሉ በሽታዎች ዙሪያ ሪፖርት ቀርቦ ምክክር እየተደረገበት ነው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ