ተላለፊና ድንገተኛ ወረርሽኝ በሽታዎችን ለመግታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ምክክር በጂንካ ከተማ ተካሔደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ድንገተኛ አደጋዎች ኦፕሬሽን ማዕከል ተላለፊና ድንገተኛ ወረርሽኝ በሽታዎች ዙሪያ የጋራ ምክክር በጂንካ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በጂንካ ከተማ ከተደራጁ የማህበራዊ ክላስተር ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ አንዱ ሲሆን ተቋማቱ ወደ ሥራ መግባታቸውን ተከትሎ፥ የድንገተኛ አደጋዎች ኦፕሬሽን ክላስተሩ ከተደራጀ በኋላ የመጀመሪያ የሆነውን ውይይት እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የልማት አጋር ድርጅቶች፣ የማዕከሉ አመራሮች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ታዬን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው በ36 ሳምንታት አፈፃፀም ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ወባ፣ ኮሌራ የምግብ እጥረት እና በሌሎችም በወረርሽኝ መልክ ሊገለፁ በሚችሉ በሽታዎች ዙሪያ ሪፖርት ቀርቦ ምክክር እየተደረገበት ነው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ