ተላለፊና ድንገተኛ ወረርሽኝ በሽታዎችን ለመግታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ምክክር በጂንካ ከተማ ተካሔደ
ሀዋሳ፡ መስከረም 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ድንገተኛ አደጋዎች ኦፕሬሽን ማዕከል ተላለፊና ድንገተኛ ወረርሽኝ በሽታዎች ዙሪያ የጋራ ምክክር በጂንካ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በጂንካ ከተማ ከተደራጁ የማህበራዊ ክላስተር ተቋማት መካከል የጤናው ዘርፍ አንዱ ሲሆን ተቋማቱ ወደ ሥራ መግባታቸውን ተከትሎ፥ የድንገተኛ አደጋዎች ኦፕሬሽን ክላስተሩ ከተደራጀ በኋላ የመጀመሪያ የሆነውን ውይይት እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የልማት አጋር ድርጅቶች፣ የማዕከሉ አመራሮች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ታዬን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው በ36 ሳምንታት አፈፃፀም ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ወባ፣ ኮሌራ የምግብ እጥረት እና በሌሎችም በወረርሽኝ መልክ ሊገለፁ በሚችሉ በሽታዎች ዙሪያ ሪፖርት ቀርቦ ምክክር እየተደረገበት ነው።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የመምህርነት ሙያ ትውልድን የመቅረፅና ሀገርን የማነፅ ታላቅ የስልጣኔና ማህበራዊ የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ ተመራቂዎች ራሳቸውን ለማብቃት መትጋት አለባቸው – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተሻሻለ የስልጠና ጥራት፣ በተጠናከረ የኢንዱስትሪ ትስስርና ተፈላጊ ሙያተኞችን በማፍራት በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ313 ሺህ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰራጭቷል – የክልሉ ግብርና ቢሮ