የፓን አፍሪካ የወባ ትንኝ ቁጥጥር 9ኛ ኮንፍራንስና አውደ ርእይ በአዲስአበባ እየተካሄደ ነው
በኮንፍረንሱ ለይ ከ36 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ተሳትፈውበታል ።
በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ህይወት ሰለሞን እንደገለጹት የወባ በሽታ በአፍሪካ 95 ከመቶ በላይ ሞትና ህመም ያስከትላል ።
ኢትዮጵያ የወባ በሽታን የመከላከሉን ሥራ ከ60 ዓመታት በላይ ስትሠራ መቆየቷንም ተመላክቷል ።
በ2015 ዓ/ም ብቻ ከ19.5 ሚሊዬን በላይ የአልጋ አጎበሮችን ማሰራጨት የተቻለ ሲሆን በተለያዩ አከባቢዎች የፀረ ወባ ትንኝ ኬሚካል ርጭት መካሄዱንም ዶክተር ህይወት አስረድተዋል ።
በኮንፍረንሱ ላይ የሚቀርቡ ጥናቶች በቀጣይ የወባን ስርጭት የመከላከሉን ሥራ በኢትዮጵያ ቢሎም በአፍሪካ አህጉር አጠናክሮ ለመቀጠል አጋዥ ግብአት ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም መሪ ሥራ አሰፈጻሚዋ ገልጻለች ።
በኮንፍራሱ በአፍሪካ በአዲስ መልክ በገባችው የወባ አስተላለፊ ትንኝ ዙሪያም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች የሚሠሩበት እንደሚሆን ተጠቁሟል ።
በ9ኛው የፓን አፍሪካ የወባ ትንኝ ቁጥጥር ጉባኤ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮችም ተሳትፈዋል ።
በአዲስአበባ ስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄ ያለው ዓመታዊ ኮንፍረንሱ እስከ ፊታችን አረብ የሚቀጥል እንደሆነም ታውቋል።
ዘጋቢ ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
የመምህርነት ሙያ ትውልድን የመቅረፅና ሀገርን የማነፅ ታላቅ የስልጣኔና ማህበራዊ የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ ተመራቂዎች ራሳቸውን ለማብቃት መትጋት አለባቸው – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተሻሻለ የስልጠና ጥራት፣ በተጠናከረ የኢንዱስትሪ ትስስርና ተፈላጊ ሙያተኞችን በማፍራት በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ313 ሺህ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰራጭቷል – የክልሉ ግብርና ቢሮ