ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን በማፍራት ረገድ የግል ትምህርት ተቋማት አስተዋጸኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ መስከረም 05/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን በማፍራት ረገድ የግል ትምህርት ተቋማት አስተዋጸኦ ከፍተኛ መሆኑን የሸኮ ወረዳ ዋና አስተዳደር አስታወቀ።
የአብሲንያ ሻይን ቢዝነስ ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በሽኮ ካምፓስ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 4 ያሰለጠናቸውን 155 ሰልጣኞችን አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 74ቱ ሴቶች ናቸው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ባለቤት አቶ አስራት አበበ ከአከባቢው ራቅ ባለ ቦታ ይማሩ የነበሩ የአከባቢው ልጆች በአቅራቢያቸው የትምህርት እድል ማግኘታቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይም የበለጠ የአከባቢውን ፍላጉት መነሻ ባደረጉ መልኩ በተለያዩ የሥልጠና መስኮች ኮሌጁ እንደሚያሰለጥን ተናግረዋል፡፡
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሪ ጉርሙ በበኩሏቸው ለኮሌጁ ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትያስተላለሁ ሲሆን ኮሌጁ የአከባቢውን ወጣቶ በማስልጠን የስራ እድል እንዲፈጥሩ በማስቻል ረገድ አጋዥ በመሆኑ ለኮሌጁ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፦ ገበየሁ ብዙአየሁ- ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
የፍትህ ተቋማት ተገልጋዩን ህብረተሰብ በሚመጥን መልኩ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ
በተገልጋይ እርካታና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ
የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑ ተጠቆመ