ጊፋታ የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻልና የአብሮነት በዓል በመሆኑ በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ ተገለጸ

ጊፋታ የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻልና የአብሮነት በዓል በመሆኑ በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ ተገለጸ

ሀዋሳ፡መስከረም 05/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጊፋታ የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻልና የአብሮነት በዓል እንደ መሆኑ በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ በየወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ገለጸ፡፡

“አዲሱ ትውልድ የጊፋታ በዓል ያከብራል” በሚል መሪ ቃል በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከወጣቱ ክፍል ጋር ውይይት ተደርጓል::

የውይይት መድረኩ ወጣቱ ትውልድ የጊፋታን በዓል ከመቼውም ጊዜ በላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ማክበር እንዳለበት የሚያስችል መሆኑን የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አይዛ ተናግረዋል፡፡

“ጊፋታ” የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻል፣ የአብሮነትና የፍቅር በዓል በመሆኑ በዓሉን በመረዳዳትና አቅም የሌላቸውን በማገዝ ማክበር እንደሚባም ተገልጿል፡፡
ወጣት በረከት ማደቦ፣ ወጣት ፀጋነሽ ኢሳያስ እና ወጣት ከተማ ፋንታ የውይይቱ ተሳታፊዎች ሲሆኑ “ጊፋታ” በዓል ባህላዊ ይዘቱን ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል::

የ”ጊፋታ”ን በዓል ለማክበር በርካታ እንግዶች ወደ ከተማችን ስለሚመጡ የውበት ስራዎችን ጨምሮ በተለያዩ ተግባራት ለይ እየተሳተፈን እንገኛለን ያሉ የውይይቱ ተሳታፊ ወጣቶች እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል::

አዘጋጅ: ተስፋሁን ሳርካ – ከዋካ ቅርንጫፍ