ጊፋታ የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻልና የአብሮነት በዓል በመሆኑ በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡መስከረም 05/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጊፋታ የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻልና የአብሮነት በዓል እንደ መሆኑ በመረዳዳት ማክበር እንደሚገባ በየወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ገለጸ፡፡
“አዲሱ ትውልድ የጊፋታ በዓል ያከብራል” በሚል መሪ ቃል በወላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ከወጣቱ ክፍል ጋር ውይይት ተደርጓል::
የውይይት መድረኩ ወጣቱ ትውልድ የጊፋታን በዓል ከመቼውም ጊዜ በላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ማክበር እንዳለበት የሚያስችል መሆኑን የቦዲቲ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አይዛ ተናግረዋል፡፡
“ጊፋታ” የሠላም፣ የእርቅ፣ የመቻቻል፣ የአብሮነትና የፍቅር በዓል በመሆኑ በዓሉን በመረዳዳትና አቅም የሌላቸውን በማገዝ ማክበር እንደሚባም ተገልጿል፡፡
ወጣት በረከት ማደቦ፣ ወጣት ፀጋነሽ ኢሳያስ እና ወጣት ከተማ ፋንታ የውይይቱ ተሳታፊዎች ሲሆኑ “ጊፋታ” በዓል ባህላዊ ይዘቱን ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል::
የ”ጊፋታ”ን በዓል ለማክበር በርካታ እንግዶች ወደ ከተማችን ስለሚመጡ የውበት ስራዎችን ጨምሮ በተለያዩ ተግባራት ለይ እየተሳተፈን እንገኛለን ያሉ የውይይቱ ተሳታፊ ወጣቶች እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል::
አዘጋጅ: ተስፋሁን ሳርካ – ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
የመምህርነት ሙያ ትውልድን የመቅረፅና ሀገርን የማነፅ ታላቅ የስልጣኔና ማህበራዊ የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ ተመራቂዎች ራሳቸውን ለማብቃት መትጋት አለባቸው – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተሻሻለ የስልጠና ጥራት፣ በተጠናከረ የኢንዱስትሪ ትስስርና ተፈላጊ ሙያተኞችን በማፍራት በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ313 ሺህ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰራጭቷል – የክልሉ ግብርና ቢሮ