ይቅርታ ካገኙ ታራሚዎች መካከል 12ቱ ሴቶች ናቸው።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሀላፊ እና የክልሉ የይቅርታ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ማቶ ማሩ እንደገለፁት የክልሉ ርዕሰ መስተደድር የኢትዮጵያውያን አዲስ አመት መግባት ምክንያት በማድረግ ለታራሚዎቹ ይቅርታ መስጠታቸውን ተናግረዋል።
ታራሚዎቹ የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈፀም ወደ ማረሚያ ተቋማት መግባታቸውን ጠቅሰው በቆይታቸውም መልካም ስነ ምግባር ያሳዩ እንደሆኑም አስረድተዋል።
በይቅርታ የተለቀቁ ታራሚዎች የበደሉትን ህብረተሰብ እና መንግስት እንዲክሱ በአንፃሩ ደግሞ ህብረተሰቡም ታራሚዎችን ተቀብሎ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል የፍትህ ቢሮ ሀላፊው።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ መስጠት እንዳለባቸው ተገለጸ
የጡት ካንሰር የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ምርመራ ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
የማታ 1፡00 ዜና 24፤ ሀዋሳ፡ ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም #ደሬቴድ – ቀጥታ ስርጭት #ዜና24 #ዜና #ደቡብቴቪ