የሲዳማ ክልላዊ መንግስት ለ1ሺህ 2 መቶ 5 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

ይቅርታ ካገኙ ታራሚዎች መካከል 12ቱ ሴቶች ናቸው።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሀላፊ እና የክልሉ የይቅርታ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ማቶ ማሩ እንደገለፁት የክልሉ ርዕሰ መስተደድር የኢትዮጵያውያን አዲስ አመት መግባት ምክንያት በማድረግ ለታራሚዎቹ ይቅርታ መስጠታቸውን ተናግረዋል።

ታራሚዎቹ የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈፀም ወደ ማረሚያ ተቋማት መግባታቸውን ጠቅሰው በቆይታቸውም መልካም ስነ ምግባር ያሳዩ እንደሆኑም አስረድተዋል።

በይቅርታ የተለቀቁ ታራሚዎች የበደሉትን ህብረተሰብ እና መንግስት እንዲክሱ በአንፃሩ ደግሞ ህብረተሰቡም ታራሚዎችን ተቀብሎ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል የፍትህ ቢሮ ሀላፊው።

ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ