ይቅርታ ካገኙ ታራሚዎች መካከል 12ቱ ሴቶች ናቸው።
የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሀላፊ እና የክልሉ የይቅርታ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ማቶ ማሩ እንደገለፁት የክልሉ ርዕሰ መስተደድር የኢትዮጵያውያን አዲስ አመት መግባት ምክንያት በማድረግ ለታራሚዎቹ ይቅርታ መስጠታቸውን ተናግረዋል።
ታራሚዎቹ የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈፀም ወደ ማረሚያ ተቋማት መግባታቸውን ጠቅሰው በቆይታቸውም መልካም ስነ ምግባር ያሳዩ እንደሆኑም አስረድተዋል።
በይቅርታ የተለቀቁ ታራሚዎች የበደሉትን ህብረተሰብ እና መንግስት እንዲክሱ በአንፃሩ ደግሞ ህብረተሰቡም ታራሚዎችን ተቀብሎ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል የፍትህ ቢሮ ሀላፊው።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ