በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ የመንግስት ተቋማት ስራ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 04/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ የመንግስት ተቋማት ስራ በይፋ ተጀምሯል፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ፣ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ዘረፍ አስተባባሪና የክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬ ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በይፋ ስራ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ሰንድቅ አለማ እና የክልሉ ሰንደቅ አለማ የመስቀል መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን በቀጣይ የክልሉ ስራ ሀላፊዎች የቢሮ ርክክብና ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በዛሬ ዕለት ስራ በወልቂጤ ከተማ የጀመረው መንግስት ተቋማት ህግ አውጭና የመስረተ ልማት ክላስተር ቢሮ መገኛ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ: ፋሲል ሀይሉ
More Stories
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ