በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ የመንግስት ተቋማት ስራ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 04/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ የመንግስት ተቋማት ስራ በይፋ ተጀምሯል፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ፣ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ዘረፍ አስተባባሪና የክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬ ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በይፋ ስራ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ሰንድቅ አለማ እና የክልሉ ሰንደቅ አለማ የመስቀል መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን በቀጣይ የክልሉ ስራ ሀላፊዎች የቢሮ ርክክብና ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በዛሬ ዕለት ስራ በወልቂጤ ከተማ የጀመረው መንግስት ተቋማት ህግ አውጭና የመስረተ ልማት ክላስተር ቢሮ መገኛ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ: ፋሲል ሀይሉ

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር