በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ የመንግስት ተቋማት ስራ በይፋ ተጀመረ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 04/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማ የመንግስት ተቋማት ስራ በይፋ ተጀምሯል፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና አፈ-ጉባዔ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎ፣ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ዘረፍ አስተባባሪና የክልሉ መንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬ ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በይፋ ስራ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ ሰንድቅ አለማ እና የክልሉ ሰንደቅ አለማ የመስቀል መርሃ ግብር የተከናወነ ሲሆን በቀጣይ የክልሉ ስራ ሀላፊዎች የቢሮ ርክክብና ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በዛሬ ዕለት ስራ በወልቂጤ ከተማ የጀመረው መንግስት ተቋማት ህግ አውጭና የመስረተ ልማት ክላስተር ቢሮ መገኛ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።
ዘጋቢ: ፋሲል ሀይሉ

More Stories
የመምህርነት ሙያ ትውልድን የመቅረፅና ሀገርን የማነፅ ታላቅ የስልጣኔና ማህበራዊ የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ ተመራቂዎች ራሳቸውን ለማብቃት መትጋት አለባቸው – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተሻሻለ የስልጠና ጥራት፣ በተጠናከረ የኢንዱስትሪ ትስስርና ተፈላጊ ሙያተኞችን በማፍራት በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ313 ሺህ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰራጭቷል – የክልሉ ግብርና ቢሮ