የጎፋ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ ተወካይ ሻለቃ በላይ ብርሃኑ እንደገለፁት የዛሬው ቀን የጀግኖች አርበኞች አባቶቻችንና የአሁኑ ትውልድ ዘመን ተሻጋሪ መስዋዕትነት የሚታወስበት ዕለት ነው፡፡
የሣውላ ከተማ ከንቲባ አቶ ኤርሚያስ ወሰኔ በበኩላቸው የመስዋዕትነት ቀንን ስናከብር ኢትዮጵያ በተሰማራችበት መስክ የድል ባለቤትና በዓለም ደረጃ በጀግንነት የምትታወቅ አገር መሆኗን ለማስታወስ መሆኑን አስረድተዋል።
ለሀገራቸው የተዋደቁ ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክሰው የህይወት መስዋዕትነት በመክፈል ሀገርን ከውጭ ወራሪ የታደጉ የጀግኖች መገኛ አገር መሆኑዋን በመረዳት የምንዘክርበትና መጭው ትውልድ ይህን ታሪክ በመማር የራሱን አሻራ የሚያሳርፍበት ቀን ነው ብለዋል፡፡
የጎፋ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ታረቀኝ አጥናፉ የመስዋዕትነት ቀን ሲከበር ለሀገር ስላም ዘብ በመሆንና የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት ማሰጠበቅ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ያነጋገርናቸው የጸጥታ አካላት ሀገር በዜጎች መሰዋዕትነት በጽናት የምትቆም በመሆኑ አሰፈላጊውን መሰዋዕትነት በመክፈል የሀገርን ጸጥታና ልማት ማረጋገጥ እንደሚገባ አንሰተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር