ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 02/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጀግና ህዝብና ትውልድ መፍጠር እንደሚቻል ታሪክን ካቆዩልን አያቶች በመማርና የከፈሉትን መስዋዕትነት በመዘከር ሀገርን ማፅናት እንደሚገባ የወላይታ ሶዶ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡
ጳጉሜን 2 የሚከበረውን የመስዋዕትነት ቀን ምክንያት በማድረግ አስተያየታቸውን ከሰጡት የወላይታ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወ/ሮ ፍሬህይወት ደመቀ፣ አቶ ምስጋናው አየለ፣ ወ/ሮ ምህረት አድማሱ እና ተመስገን አደለ፤ ኢትዮጵያ ይህን የመስዋዕትነት ቀን የምታከብረው ያሳለፈችው አኩሪ ታሪክ ስላላት ነው ያሉት ነዋሪዎቹ ታሪክን ለትውልድ ከማሻገር አንፃር ትውልዱም ሀገሩን ጠብቆ ለማቆየት የዛሬዋን ኢትዮጵያ ትናንት መስዋዕትነት ከፍለው ያቆዩን አርበኛ አያቶች ማሰብና መዘከር ይገባል ብለዋል፡፡
ወጣቱ ትውልድ በተሰማራበት ዘርፍ ጥንካሬና ታታሪነቱን በማጠናከር ለሀገሩ ሊከፍለው የሚገባውን መስዕዋትነት ለመክፈል ዝግጁ ሊሆን እንደሚገባና ለመጭው ትውልድም መልካም ታሪክን ፅፎ ማቆየት እንዳለበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ትዉልዱ የተጣለበትን ኃላፊነት በታማኝነት በመወጣትም ሀገርን ከሚያፈርሱ ተግባራት በመጠበቅ በመስዋዕትነት የተገኘዉን አንድነት ማስቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።
መስዋዕትነት የራስን ህይወት አሳልፎ የሚሰጥ ትልቅ ስጦታ በመሆኑ ለሀገሪቷ መስዕዋትነት የከፈሉ አያቶቻችን ወደፊትም አሁንም እየከፈሉ ላሉ አካላት ከጎናቸው በመቆም እንደሚደግፉና የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ “በመስዋዕትነት የምትፀና ሀገር” በሚል የሚከበረውን ጳጉሜን 2 የመስዋዕትነት ቀን ዕለት ለሀገራቸው መስዋዕትነት ከፍለው ያለፉ አያቶችን በመዘከርና በማሰብ እያከበሩ መሆናቸውን ነው ነዋሪዎቹ የገለፁት፡፡
ዘጋቢ፡ ብዙነሽ ዘውዱ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ