የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ባዕድ ነገሮችን በመቀላቀል የሚሸጡና ሐሰተኛ የብር ኖቶችን የሚያዘዋዉሩ ሰዎችን ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት እንዲያሳዉቅ የጂንከ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ጥሪ አቀረበ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 02/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ባዕድ ነገሮችን በመቀላቀል የሚሸጡና ሐሰተኛ የብር ኖቶችን የሚያዘዋዉሩ ግለሰቦችን ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ የጂንከ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ጥሪ አቀረበ፡፡
የከተማዉ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሽብሩ አማረ እንደገለጹት መጪዉን አዲስ አመት ምክንያት በማድረግ አርሶና አርብቶ አደሩ በጥራት ያፈራቸዉን ንብረቶች ወደ ገበያ በሚያቀርቡበት ወቅት በሀሰተኛ የብር ኖቶች አዘዋዋሪ ሕገ- ወጥ ነጋዴዎች እንዳይታለሉ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ነዉ ብለዋል፡፡
ከበአል ግብይት ጋር ተያይዞ ባዕድ ነገሮችን በመቀላቀል በርካሽ ዋጋ የሚያቀርቡ ስግብግብ ነጋዴዎች ስለሚኖሩ ሸማቾች ሲገበያዩ በጥራት ዙርያ ትኩረት በማድረግ ማረጋገጥ እንዳለባቸዉም ፖሊስ አዛዡ አሳስበዋል፡፡
ከዚህ በፊት ከ18 ሺህ ብር በላይ ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ሲያዘዋዉሩ በህግ ቁጥጥር ስር የዋሉ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች መኖራቸዉም በመግለፅ፡፡
ፖሊስ አዛዡ አያይዘዉም መጪዉን የአዲስ ዓመት በማስመልክት የሚፈፀሙ ወንጀሎችና ሕገ- ወጥ ስግብግብ ነጋዴዎችን በማጋለጥ ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር እንዲተባበር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሁሴን አለሙ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ
ማህበራዊ ሚዲያ ጊዜና ቦታ ሳይገድበው መረጃን በፍጥነት ተደራሽ ስለሚያደርግ ተጠቃሚዎች ትክክለኛ እና ተአማኒነት ያለውን መረጃ ማሰራጨት ይጠበቅባቸዋል – ዶ/ር በኃይሉ ገ/ማሪያም
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ