የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ባዕድ ነገሮችን በመቀላቀል የሚሸጡና ሐሰተኛ የብር ኖቶችን የሚያዘዋዉሩ ሰዎችን ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት እንዲያሳዉቅ የጂንከ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ጥሪ አቀረበ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 02/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ባዕድ ነገሮችን በመቀላቀል የሚሸጡና ሐሰተኛ የብር ኖቶችን የሚያዘዋዉሩ ግለሰቦችን ሕብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ የጂንከ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ጥሪ አቀረበ፡፡
የከተማዉ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሽብሩ አማረ እንደገለጹት መጪዉን አዲስ አመት ምክንያት በማድረግ አርሶና አርብቶ አደሩ በጥራት ያፈራቸዉን ንብረቶች ወደ ገበያ በሚያቀርቡበት ወቅት በሀሰተኛ የብር ኖቶች አዘዋዋሪ ሕገ- ወጥ ነጋዴዎች እንዳይታለሉ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ነዉ ብለዋል፡፡
ከበአል ግብይት ጋር ተያይዞ ባዕድ ነገሮችን በመቀላቀል በርካሽ ዋጋ የሚያቀርቡ ስግብግብ ነጋዴዎች ስለሚኖሩ ሸማቾች ሲገበያዩ በጥራት ዙርያ ትኩረት በማድረግ ማረጋገጥ እንዳለባቸዉም ፖሊስ አዛዡ አሳስበዋል፡፡
ከዚህ በፊት ከ18 ሺህ ብር በላይ ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ሲያዘዋዉሩ በህግ ቁጥጥር ስር የዋሉ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች መኖራቸዉም በመግለፅ፡፡
ፖሊስ አዛዡ አያይዘዉም መጪዉን የአዲስ ዓመት በማስመልክት የሚፈፀሙ ወንጀሎችና ሕገ- ወጥ ስግብግብ ነጋዴዎችን በማጋለጥ ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር እንዲተባበር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሁሴን አለሙ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ