ሀዋሳ: ጳጉሜ 01 /2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን የአገልጋይነት ቀን እየተከበረ ነው፡፡
የአገልጋይነት ቀን በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ በተለያየ ዝግጅት እየተከበረ ሲሆን እለቱን አስመልክተው በጤና ተቋማት እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሀም መጫ ተመልክተዋል::
ሀገራችንን ከልብ በቀናነት የምናገለግልበት ቀን ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው እርካታችንም የተገልጋዩ እርካታ ላይ የሚመሰረት ነው ብለዋል::
የአገልጋይነት ቀን መከበሩ ታታሪዎችን ይበልጥ የሚያነሳሳ እና ለሌሎችም አርዓያ በመሆን ለሀገር የተሻለ ሥራ ለማበርከት ያስችላል ብለዋል::
እለቱ ትልቅ ዓላማ ያነገበ በመሆኑ ለተያዘው ሀገራዊ ለውጥ ሁሉም የሚጠበቅበትን እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል::
እነዚህ የጳጉሜ ቀናት የሚያስተላልፉትን መልዕክት ሚዲያው በሚገባ ለህዝብ በማድረስ አዎንታዊ አስተዋጽዖ ሊያበረክት እንደሚገባ የገለፁት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አምሪያ ሲራጅ ናቸው::
አገልግሎት መስጠት የአንድ ቀን ተግባር ብቻ ባለመሆኑ ዘወትር ትጋትና ታታሪነት መላበስ እንደሚገባም አስገንዝበዋል::
በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ስያሜዎች የሚከበሩ የጳጉሜ ቀናት በተመሳሳይ በክልሉ በተጠናከረ መልኩ ይከበራል ብለዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ