መገናኛ ብዙሐን ለብሔራዊ ምክክር መሣካት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 30/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) መገናኛ ብዙሐን ለብሔራዊ ምክክር መሣካት የበኩላቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሐን ምክር ቤት አሳሰበ።
ተቋሙ በብሔራዊ ምክክር እና በጋዜጠኝነት ስነ ምግባር መርሆዎች ዙሪያ ለጋዜጠኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
የመገናኛ ብዙሐን ባለሙያዎች በሚሠሯቸው ዘገባዎች ለአገራዊ አንድነት ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ተብሏል።
ጋዜጠኞች ከየትኛውም ተጽዕኖ ነጻ ሆነው በሚዛናዊነትንና ገለልተኛነት መርህ ተከትለው መሥራት እንዳለባቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሐን ምክር ቤት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሠረት አታላይ አሳስበዋል።
የመገናኛ ብዙሐን የሚያሰራጯቸው መረጃዎች ሚዛናዊ እና ገለልተኛ ሆነው ለአገራዊ አንድነት እና ሠላም መጠበቅ ፋይዳ ያላቸው ሊሆኑ እንደሚገባ ስልጠና የሰጡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት መምህር ዶ/ር አብዲሳ ዘርአይ ናቸው።
በስልጠና መድረኩ ላይ ከደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪን ድርጅት አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ፣ ከወላይታ ቴሌቪዥን እና ከኢዜአ የተጋበዙ የሚዲያ ባለሙያዎች ተሣታፊ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ