መገናኛ ብዙሐን ለብሔራዊ ምክክር መሣካት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 30/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) መገናኛ ብዙሐን ለብሔራዊ ምክክር መሣካት የበኩላቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሐን ምክር ቤት አሳሰበ።
ተቋሙ በብሔራዊ ምክክር እና በጋዜጠኝነት ስነ ምግባር መርሆዎች ዙሪያ ለጋዜጠኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
የመገናኛ ብዙሐን ባለሙያዎች በሚሠሯቸው ዘገባዎች ለአገራዊ አንድነት ፋይዳ ባላቸው ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ተብሏል።
ጋዜጠኞች ከየትኛውም ተጽዕኖ ነጻ ሆነው በሚዛናዊነትንና ገለልተኛነት መርህ ተከትለው መሥራት እንዳለባቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሐን ምክር ቤት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሠረት አታላይ አሳስበዋል።
የመገናኛ ብዙሐን የሚያሰራጯቸው መረጃዎች ሚዛናዊ እና ገለልተኛ ሆነው ለአገራዊ አንድነት እና ሠላም መጠበቅ ፋይዳ ያላቸው ሊሆኑ እንደሚገባ ስልጠና የሰጡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት መምህር ዶ/ር አብዲሳ ዘርአይ ናቸው።
በስልጠና መድረኩ ላይ ከደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪን ድርጅት አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ፣ ከወላይታ ቴሌቪዥን እና ከኢዜአ የተጋበዙ የሚዲያ ባለሙያዎች ተሣታፊ ናቸው።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ