የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ዲላ ከተማ ገቡ
በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራ ልዑክ ወደ ከተማዋ ሲደርሱ በጌዴኦ ዞን እና የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የግብርና እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች የክልል ቢሮዎች መቀመጫ የሆነችው የዲላ ከተማ ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ዛሬ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ከተማዋ ሲደርሱ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይለማርያም ተስፋዬ፣ የቀድሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ