የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ዲላ ከተማ ገቡ
በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራ ልዑክ ወደ ከተማዋ ሲደርሱ በጌዴኦ ዞን እና የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የግብርና እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች የክልል ቢሮዎች መቀመጫ የሆነችው የዲላ ከተማ ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ዛሬ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ከተማዋ ሲደርሱ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይለማርያም ተስፋዬ፣ የቀድሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ