የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ዲላ ከተማ ገቡ
በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራ ልዑክ ወደ ከተማዋ ሲደርሱ በጌዴኦ ዞን እና የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የግብርና እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች የክልል ቢሮዎች መቀመጫ የሆነችው የዲላ ከተማ ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ዛሬ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ከተማዋ ሲደርሱ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይለማርያም ተስፋዬ፣ የቀድሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ
More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ ከአካባቢ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ አንድነትና ሠላም እንዲረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝ የኣሪ ዞን የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገለፀ
የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
የሀድያ የልማት እድገት፣ አንድነትና የመተባበር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው