የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ዲላ ከተማ ገቡ
በርዕሰ መስተዳድሩ የተመራ ልዑክ ወደ ከተማዋ ሲደርሱ በጌዴኦ ዞን እና የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የግብርና እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ሌሎች የክልል ቢሮዎች መቀመጫ የሆነችው የዲላ ከተማ ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ዛሬ እየተካሄደ ነው።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ወደ ከተማዋ ሲደርሱ የክልሉ ግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይለማርያም ተስፋዬ፣ የቀድሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንዲሁም ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

More Stories
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ