24 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ ነው
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) መንግስት የኑሮ ወድነትን ለማሻሻል እና ገበያን ለማረጋጋት ተከታታይነት ያለው እርምጃ አንደሚወስድ ቃል በገባው መሠረት 24 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ የተለያዩ የአገራችን ክፍሎች እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የምግብ ዘይቱ በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አማካኝነት በሁለት ምዕራፍ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ሲሆን፣ ይህ የፍጆታ ዕቃ በዋነኝነት የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል እና ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት ታስቦ በመንግስት ግዢ የተደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በማጓጓዝ ስራው የጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እንዲሁም ከኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ጋር በመቀናጀት በተቀላጠፈ መልኩ እየተሰራ እንደሆነ እና በመጀመሪያ የኦፕሬሽን ምዕራፍ 11 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ መላክ መቻሉ ተገልጿል።
በሁለተኛው ምዕራፍ 13 ሚሊዮን የምግብ ዘይት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ አገር ቤት እንዲገባ ብርቱ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘ መረጃ ያመለክታል::
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ