24 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ ነው
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) መንግስት የኑሮ ወድነትን ለማሻሻል እና ገበያን ለማረጋጋት ተከታታይነት ያለው እርምጃ አንደሚወስድ ቃል በገባው መሠረት 24 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ የተለያዩ የአገራችን ክፍሎች እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የምግብ ዘይቱ በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አማካኝነት በሁለት ምዕራፍ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ሲሆን፣ ይህ የፍጆታ ዕቃ በዋነኝነት የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል እና ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት ታስቦ በመንግስት ግዢ የተደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በማጓጓዝ ስራው የጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ፣ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እንዲሁም ከኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ጋር በመቀናጀት በተቀላጠፈ መልኩ እየተሰራ እንደሆነ እና በመጀመሪያ የኦፕሬሽን ምዕራፍ 11 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ መላክ መቻሉ ተገልጿል።
በሁለተኛው ምዕራፍ 13 ሚሊዮን የምግብ ዘይት በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ አገር ቤት እንዲገባ ብርቱ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘ መረጃ ያመለክታል::
More Stories
በስብዕና ግንባታ ስራ ላይ በማተኮር በስነ-ምግባር የታነፀ ዜጋን ለማፍራት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአረጋዉያን ያስገነባዉን የመኖሪያ እና እንክብካቤ ማዕከል ስራ አስጀመረ
የትምህርት ዘርፍ መጠናከር ሀገሪቱ ወደ አዲስ የስልጣኔ ማማ ለመድረስ ለምታደርገው ጉዞ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ አስታወቀ