የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የነሐሴ 10/2015 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡-

የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የነሐሴ 10/2015 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡-

👉መንግስት የኑሮ ወድነትን ለማሻሻል እና ገበያን ለማረጋጋት ተከታታይነት ያለው እርምጃ አንደሚወስድ ቃል በገባው መሠረት 24 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ተገለጸ።

👉የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡

👉በክልሉ 697 የተለያዩ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ ተናገሩ።

👉ከ84 ሚሊየን ብር በላይ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የሀዲያ ዞን ስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ጥምረት አስታወቀ።

👉ኢትዮጵያ ከፊሊፒንስ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሻ በፊሊፒንስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሰየሙት ደሴ ዳልኬ ገለጹ።

👉በቤንች ሸኮ ዞን በተያዘው በጀት ዓመት በህብረተሰብ ተሳትፎ የ60 ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።

👉በድሬዳዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ከ99 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡