የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የነሐሴ 10/2015 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡-
👉መንግስት የኑሮ ወድነትን ለማሻሻል እና ገበያን ለማረጋጋት ተከታታይነት ያለው እርምጃ አንደሚወስድ ቃል በገባው መሠረት 24 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ተገለጸ።
👉የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡
👉በክልሉ 697 የተለያዩ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ ተናገሩ።
👉ከ84 ሚሊየን ብር በላይ የመንግስትና የህዝብ ሀብት ከምዝበራ ማዳን መቻሉን የሀዲያ ዞን ስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ጥምረት አስታወቀ።
👉ኢትዮጵያ ከፊሊፒንስ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እንደምትሻ በፊሊፒንስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሰየሙት ደሴ ዳልኬ ገለጹ።
👉በቤንች ሸኮ ዞን በተያዘው በጀት ዓመት በህብረተሰብ ተሳትፎ የ60 ትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ታቅዶ ወደተግባር መገባቱን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
👉በድሬዳዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ከ99 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

More Stories
7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ እንዲሆን ሰፊ ተግባራት መከናወናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በፓርቲው መሪነት በልማት፣ በመልካም አስተዳደር እና በፖለቲካው ዘርፍ አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል – አቶ ፍቅሬ አማን
በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ በመማር ማስተማር ዘርፍ እየተመዘገቡ የሚገኙ ለወጦች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ