ቢሮው በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬት ስራ በማጠናቀቅ የይዞታ ማረጋገጫ ለአርሶአደሮች አስረከበ

ቢሮው በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬት ስራ በማጠናቀቅ የይዞታ ማረጋገጫ ለአርሶአደሮች አስረከበ

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ቢሮ በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ በጂኦ ስፓሻል ዘርፍ በCAM-LA ፕሮጀክት የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ልኬት ስራ አጠናቆ የይዞታ ማረጋገጫ ለአርሶአደሮች አስረክቧል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰብስቤ ቡናቤ በመርሃ ግብሩ እንደተናገሩት፣ ቢሮው የአርሶአደሩን የመሬት ይዞታ ባለቤትነትን በማረጋገጥ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰራ ነው።

‎እንደ አቶ ሰብስቤ ገለጻ፤ የመሬት ይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫው ባለንብረትነትን ከማረጋገጥ በተጨማሪ አርሶአደሮች ተበድረው ሀብት ማፍራት የሚችሉበት ነው።

‎የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪና ተወካይ አቶ ዳንኤል ሽፈራው በበኩላቸው፤ የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር እና የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ በሚከናወኑ ተግባራት ውጤት እየተመዘገቡ ናቸው ብለዋል።

‎አሁን ላይ በመሬት ልኬት ዘርፍ እየተሰራ ያለው ተግባር አበረታች መሆኑንም አቶ ዳንኤል አመላክተዋል።

‎የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ ታደሰ፤ ልኬቱ ለአርሶአደሮች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የጎላ ፋይዳ እንዳለው ነው የተናገሩት።

‎ልኬቱ ተጠናቆላቸው የማረጋገጫ ደብተር የወሰዱ አርሶአደሮች በበኩላቸው፤ ከመሬት ባለቤትነት ጋር ተያይዘው ይመጡ የነበሩ ችግሮችን የፈታና ተበድረው ራሳቸውን እንዲቀይሩ በር የከፈተ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

‎ዘጋቢ: እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን