አትሌት ልቅና አምባው ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳልያ አስገኘች!
በዴንማርክ ኮፐንሀገን እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም አትሌቲክስ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አትሌት ልቅና አምባው ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አስገኝታለች።
በሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ውድድር በመሳተፍ ነው አትሌት ልቅና አምባው ለሀገሯ የወርቅ ሜዳልያ ያሳካችው።
አትሌቷ 14 ደቂቃ ከ41 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት ውድድሩን በማጠናቀቅ የዓመቱን ምርጥ ሰዓቷን ማስመዝገብ ችላለች።
ረፋድ ላይ በተደረገ የአንድ ማይል ውድድር አትሌት ፍሬወይኑ ሀይሉ ሁለተኛ በመውጣት ለኢትዮጲያጰየብር ሜዳልያ ማሳካት ችላለች።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
ቶትንሃም በአስቶንቫላ ተሸነፈ
አባቱን በደስታ ያዘለለው ልጅ
ሆዜ ሞሪንሆ እና ዲዬጎ ሲምዮኔ ከ12 ዓመታት በኋላ በማድሪድ ደርቢ ይፋለማሉ