ጷጉሜ 4 የህብር ቀንን በማስመልከት ለአቅመ ደካሞች የበዓል ድጋፍ ተደረገ
ጷጉሜ 4 የህብር ቀንን በማስመልከት የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር ከወረዳው የተለያዩ ቀበሌያት ለተውጣጡ አቅመ ደካሞች የበዓል ድጋፍ አደረገ።
ድጋፉን ያደረገው የይርጋጨፌ ወረዳ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት፥ በዓሉን በማሰብ በችግር ውስጥ የሚገኙ ወገኖችን ለመርዳት ድጋፍ መደረጉ ተገልጿል።
የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ፥ ጷጉሜ 4 የህብር ቀንን ስናከብር ካለን ላይ ብቻ ሳይሆን ከሌለንም ቢሆን በመካፈልና እርስ በርስ በመደጋገፍ በዓሉን ማክበር እንደሚገባ ገልጸዋል።
በዓሉ ያለው ለሌለው በመስጠት፣ ችግረኛ ወገኖችን በማሰብና በመደጋገፍ እንዲከበር ጥሪ ያቀረቡት አስተዳዳሪው፥ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለሚከሰቱ ችግሮችም ፈጣሪ ዝናብ በምህረቱ እንዲያወርድ ሁሉም ዜጋ በጸሎትና በምልጃ እንዲሳተፍ ጠይቀዋል።
የይርጋጨፌ ወረዳ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት ያያ በበኩላቸው፣ ከወረዳው የተለያዩ ቀበሌያት ለተወጣጡ አቅመ ደካሞች የበዓል ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።
የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና ከሚኖረን ላይ በመካፈል በዓሉን በህብረት ማክበር እንደሚገባም ለህብረተሰቡ ጥሪ አቅርበዋል።
የበዓሉ ድጋፍ የተደረገላቸው የማህበረሰብ ክፍሎችም ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፣ ሌሎችም በየአካባቢያቸው ተመሳሳይ የመደጋገፍ ተግባር እንዲያከናውኑ ጠይቀዋል።
ዘጋቢ: ውብሸት ካሳሁን – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
ጷጉሜ 4 የህብር ቀንን በማስመልከት ለአቅመ ደካሞች የበዓል ድጋፍ ተደረገ

More Stories
የልማት መጓተትን ለማስቀረትና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በህብረት ተደጋግፎ መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ
ከፋፋይ ከሆኑ አጀንዳዎች በመራቅ ህብረታችንን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
በሀድያ ዞን ጎምቦራ ወረዳ ሀብቾ ከተማ ነዋሪ ለሆኑ አንዲት አቅመ ደካማ እናት የመኖሪያ ቤት ርክክብ ተደረገ