በደቡብ ሬዲዮ እና ቴለቪዥን ድርጅት ዋካ ቅርንጫፍ FM 93.4 የተመሠረተበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ሰራተኞቹ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ሬዲዮ እና ቴለቪዥን ድርጅት ዋካ ቅርንጫፍ ሰራተኞች ዋካ FM 93.4 የተመሠረተበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
በተቋሙ ቅጥር ግቢ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ለአካባቢ ጥበቃ የሚኖራቸው ፋይዳም ጉልህ መሆኑ ተገልጿል።
የሚድያ ተቋማት የተሰጣቸውን ተግባራት ብቻ ሳይሆን እንዲህ ባሉ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ለሀገራዊ ጥሪ የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ አዲስዓለም ታዬ – ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ