በደቡብ ሬዲዮ እና ቴለቪዥን ድርጅት ዋካ ቅርንጫፍ FM 93.4 የተመሠረተበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ሰራተኞቹ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ሬዲዮ እና ቴለቪዥን ድርጅት ዋካ ቅርንጫፍ ሰራተኞች ዋካ FM 93.4 የተመሠረተበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
በተቋሙ ቅጥር ግቢ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ለአካባቢ ጥበቃ የሚኖራቸው ፋይዳም ጉልህ መሆኑ ተገልጿል።
የሚድያ ተቋማት የተሰጣቸውን ተግባራት ብቻ ሳይሆን እንዲህ ባሉ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ለሀገራዊ ጥሪ የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ አዲስዓለም ታዬ – ከዋካ ቅርንጫፍ
More Stories
በኩታ ገጠም እየተከናወነ ባለው የቡና እና ሌሎች ፍራፍሬ ምርት ተከላ ኢኒሼቲቭ የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት በአጭር ጊዜ እያሳደገ መምጣቱን በሀላባ ዞን የዌራ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ከደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች እስከአሁን ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን በካፋ ዞን የቢጣ ወረዳ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ህብረት ስራ ማህበራት በተደራጁበት ዓላማ ለአባሎቻቸው የተሟላ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ በጠንካራ አደረጃጀትና ጤናማ የፋይናንስ ሥርዓት ሊደገፉ እንደሚገባ ተመላከተ