በደቡብ ሬዲዮ እና ቴለቪዥን ድርጅት ዋካ ቅርንጫፍ FM 93.4 የተመሠረተበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ሰራተኞቹ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ሬዲዮ እና ቴለቪዥን ድርጅት ዋካ ቅርንጫፍ ሰራተኞች ዋካ FM 93.4 የተመሠረተበትን 14ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
በተቋሙ ቅጥር ግቢ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ለአካባቢ ጥበቃ የሚኖራቸው ፋይዳም ጉልህ መሆኑ ተገልጿል።
የሚድያ ተቋማት የተሰጣቸውን ተግባራት ብቻ ሳይሆን እንዲህ ባሉ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ለሀገራዊ ጥሪ የበኩላቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።
ዘጋቢ፡ አዲስዓለም ታዬ – ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን ተከትሎ የምስጋናና የዕውቅና መርሃ-ግብር ተካሄደ
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ