በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል ያለውን የመረጃ፣ የቢዝነስና የመሰረተ ልማት ትብብር የሚያጠናክር ስምምነት ተፈረመ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል ያለውን የመረጃ፣ የቢዝነስና የመሰረተ ልማት ትብብር የሚያጠናክሩ ስምምነቶች ተፈረሙ። ስምምነቶቹ በሩሲያ አፍሪካ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ በሚገኘው የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን አባላት የተፈረሙ ናቸው ተብሏል።
በኢትዮጵያና በሩሲያ መካከል አለም አቀፍ የመረጃ ደህንነትን በተመለከተ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋና የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ናቸው።
ስምምነቱ በአለም አቀፍ ደረጃ የመረጃ ደህንነት ዘርፍ ላይ አቅምን ለመገንባት፤ የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ እንዲሁም የመሰረተ ልማትና የቴክኖሎጂ አቅምን በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው።
የሁለቱን ሃገራት የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ማሳደግ ያለመው አንዱ ነው።
ስምምነቱን የፈረሙት የሩሲያ የትራንስፖርት ሚኒስትር ኢጎር ቻሊክ ሩሲያ ከአፍሪካ ሃገራት ጋር ያላትን ትስስር ለማጠናከር የኢትዮጵያ አየርመንገድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ እና በሩሲያ የጉምሩክ አገልግሎት ሃላፊ ሩስላን ዳቪዶፍ መካከል የተፈረመው ስምምነትም በሁለቱ ሃገራት መካከል በዘርፉ ያለውን የክፍያና አገልግሎት ስርአት ለማዘመን የሚያስችል እንደሚሆን ተነግሯል።
በተጨማሪም ስምምነቱ የኢትዮጵያና የሩሲያን የንግድ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያሰችል ነው።

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ