የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶች ጤናና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የ2018 ባጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ይገኛል
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ፥ በ2018 ባጀት ዓመት የእናቶች፣ የህፃናትና የጨቅላ ህፃናት ጤናና የስርዓተ ምግብ አገልግሎት የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡን ጠቁመዋል::
በዚህም ካላፈው ባጀት ዓመት የእናቶች እና የህፃናት የሞት ምጣኔን በ3 ነጥብ 9 በመቶ በማሳደግ የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል ብለዋል::
የህብረተሰቡ የጎላ ተሣትፎ ለዘርፉ ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ስለማበርከቱም አቶ አሸናፊ ገልፀዋል::
በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል::
ዘጋቢ: አብዱልሰመድ አወል – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአርሶ አደሩን የመሬት ሀብት ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የከተማ አስተዳደሩ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽህፈት ቤት ወጣቶችን በማህበር በማደራጀት የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ
በሀገራችን ዘላቂ ሠላም ለማስፈን እና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር የጎላ ፋይዳ እንዳለው አንዳንድ የኮንሶ ዞን ነዋሪዎች ተናገሩ