የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶች ጤናና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የ2018 ባጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ይገኛል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶች ጤናና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የ2018 ባጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ይገኛል

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮው ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ፥ በ2018 ባጀት ዓመት የእናቶች፣ የህፃናትና የጨቅላ ህፃናት ጤናና የስርዓተ ምግብ አገልግሎት የተሻለ አፈፃፀም መመዝገቡን ጠቁመዋል::

በዚህም ካላፈው ባጀት ዓመት የእናቶች እና የህፃናት የሞት ምጣኔን በ3 ነጥብ 9 በመቶ በማሳደግ የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል ብለዋል::

የህብረተሰቡ የጎላ ተሣትፎ ለዘርፉ ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ስለማበርከቱም አቶ አሸናፊ ገልፀዋል::

በመድረኩ የክልሉ፣ የዞን እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል::

ዘጋቢ: አብዱልሰመድ አወል – ከሆሳዕና ጣቢያችን