የተቀናጀ መሬት አጠቃቀም ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግና የማኅበረሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በሳይንሳዊ ጥናት የታገዘ ተግባር እየተከናወነ ነው
የተቀናጀ መሬት አጠቃቀም ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግና የማኅበረሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በሳይንሳዊ ጥናት የታገዘ ተግባር እያከናወነ እንደሚገኝ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ፎለር ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አስታወቀ።
በይርጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ፎለር ፕሮጀክት በተቀናጀ መሬት አጠቃቀም ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በውይይት መድረኩ በወረዳው በሚታየው የመሬት አጠቃቀም ተግዳሮትና መፍትሄ ላይ ያተኮረ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
የውይይት መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ድጋፌ ሙላቱ እንደገለጹት፤ መሬት ለትውልድ የሚተላለፍ ሃብት ስለሆነ አጠቃቀሙ በጥናት ላይ በተመሠረተ መልኩ መሆን አለበት።
በወረዳው ያለው መሬት ከህዝብ ቁጥር ጋር ባልተጣጣመበት ሁኔታ ቀጣይነት ያለው ልማት ስለማይታሰብ መፍትሄ የሚጠቁም ጥናት እንደሆነ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ፎለር ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አስተባበሪ አቶ አለምበጁ ክፍሌ ገልጸዋል።
ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል አርሶአደር ሽፈራዉ ተጫነ እና ኢያሱ ደያሶ፤ በሚያገኙት ግንዛቤ ምርታማነታቸው እየጨመረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በመድረኩ የግብርና ምርታማነትን የሚያሻሽል የተቀናጀ የመሬት አያያዝና አስተዳደር ዕቅድ ቀርቦ ባለድርሻ አካላት የመግባቢያ ፊርማ ተፈራርመዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል ትዕግሥቱ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የተቀናጀ መሬት አጠቃቀም ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግና የማኅበረሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በሳይንሳዊ ጥናት የታገዘ ተግባር እየተከናወነ ነው

More Stories
አጫጭር የሙያ ክህሎት ስልጠና ማግኛታቸው በሚሰማሩበት የውጭ ሀገራት ሁሉ ተግባራቸውን እንዲወጡ እንደሚያስችላቸው በሆሳዕና ከተማ የሚገኙ ሰልጣኞች ተናገሩ
የማዕድን ሀብቶችን ከህገ ወጥ ደላላና የኮንትሮባንድ ንግድ ለመግታት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
በትራንስፖርትና መንገድ ልማት ዙሪያ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ