ውጤታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማከናወን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል- የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ውጤታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማከናወን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር አሳሰበ፡፡
የዘንድሮውን የወጣቶች የክረም ወራት በጎ ፈቃድ አገለግሎት አስመልክተው የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዞኑ 2015 በጀት ዓመት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገለግሎት ለማከናወን የ2014 አፈፃፀም በመገመገም ወደ ተግባር መገባቱን የዞኑ ዋና አስተዳደር አቶ ቀበሌ መንገሻ አስታውቀዋል፡፡
በመርሀግብሩ ከ10 በላይ የሆኑ የተለያዩ ተግባራቶች ይከወናሉ ያሉት ኃላፊው የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ በትኩረት የሚሠራበት መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
አመራሩ ለተግባሩ ዕገዛ በማድረግ በኩል ከዞን ጀምሮ ከተሠራ በየዘርፉ እምርታዊ ለውጥን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አብዲሳ ዮናስ- ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕብረተሰቡ በነፃነት ተሳትፎ ያደረገበት መሆኑ ተገለጸ