ውጤታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማከናወን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል- የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ውጤታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማከናወን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር አሳሰበ፡፡
የዘንድሮውን የወጣቶች የክረም ወራት በጎ ፈቃድ አገለግሎት አስመልክተው የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዞኑ 2015 በጀት ዓመት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገለግሎት ለማከናወን የ2014 አፈፃፀም በመገመገም ወደ ተግባር መገባቱን የዞኑ ዋና አስተዳደር አቶ ቀበሌ መንገሻ አስታውቀዋል፡፡
በመርሀግብሩ ከ10 በላይ የሆኑ የተለያዩ ተግባራቶች ይከወናሉ ያሉት ኃላፊው የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ በትኩረት የሚሠራበት መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
አመራሩ ለተግባሩ ዕገዛ በማድረግ በኩል ከዞን ጀምሮ ከተሠራ በየዘርፉ እምርታዊ ለውጥን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አብዲሳ ዮናስ- ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ