የተስተካከለ የአየር ንብረት እንዲኖር ችግኞችን የመትከል ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሁሉም አካባቢ የተስተካከለ የአየር ጸባይ እንዲኖር ለማስቻል ችግኞችን የመትከል ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ።
የደቡብ ኦሞ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ቆላማ አካባቢ በሆነው ሐመር ወረዳ ቱርሚ ከተማ አስተዳደር በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
በተከላ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ ለአካባቢው ምቹ ስነምህዳር ያላቸውን ችግኞችን የመትከል ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
ሐመር ወረዳ ቱርሚ ከተማና አካባቢ ሞቃታማና ቆላማ የአየር ፀባይ ያለበት ሲሆን ለአካባቢው ምቹ የሆኑ ችግኞች መተከላቸውን ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።
በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የአንድ ቀን ጀምበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደዞን ከ1 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን አቶ ንጋቱ አስታውሰው ተግባሩ በሁሉም አካባቢ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ ግብር ጭምር ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
እንደዓለም ያለውን የአየር ብክለትና ተጽእኖ ለማስቀረት ችግኝ መትከልና የአካባቢ ጥበቃን ማረጋገጥ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ስለመሆኑም ዋና አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል።
በቱርሚ ከተማ አስተዳደር በነበረው ተከላ መርሐ ግብር የተሳተፉ አካላትም አካባቢው ሞቃታማ በመሆኑ ለሰው ልጆችም ይሁን ለእንስሳት የአካባቢ ጥበቃ ወሳኝ በመሆኑ ችግኞችን እየተከሉ አንደሚገኙ ገልፀው የተተከሉት ችግኞችም ፀድቀው ለተፈለገው አላማ እንዲውል እንደሚንከባከቡም አረጋግጠዋል ።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ-ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በክረምት የተከናወኑ የወጣቶች በጎ ተግባራት ከ180 ሚሊየን ብር በላይ ከመንግስት ሊወጣ የነበረ ወጪ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የችሎት መዝገብ ስራ በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የደንበኞቹን እርካታ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ገለፀ
የፀጥታና የደህንነት ስጋቶችን በጋራ በመታገል ለሁለንተናዊ የሀገሪቱ ሠላም በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ ገለፁ