በ2018 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ሲዳማ ቡናን 2ለ0 በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን ሆኗል።
በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ለወልዋሎ የማሸነፊያ ጎሎችን ኮንካኒ ሀፊዝ እና ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው በየነ ባንጃው ከመረብ አሳርፈዋል።
በአሰልጣኝ ግርማ ታደሰ የሚመራው ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ በቀጣይ ኢትዮጵያን ወክሎ በካፍ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ይሳተፋል።
የፕሪምየር ሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና በበኩሉ በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ የሚሳተፍ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ሲዳማ ቡናን በማሸነፍ የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ

More Stories
ማንቸስተር ዩናይትድ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
ማንቸስተር ዩናይትድ አንድሬ ሳንቶስን አስፈረመ
የ2018 የCBE የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ውድድርን በማሸነፍ ሁለት ዋንጫ ላነሳው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ክልሉ ያዘጋጀውን የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 06/2018 ከቀኑ 12፡00 ጀምሮ በሀዋሳ ሀይሌ ሪዞርት ይካሄዳል።