አርሰናል ግብ ጠባቂ ሊያስፈርም ነው

አርሰናል ግብ ጠባቂ ሊያስፈርም ነው

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል አዲስ ግብ ጠባቂ ወደ ስብስቡ ለመቀላቀል ተዘጋጅቷል።

መድፈኞቹ ወደ ስብሰባቸው ለመቀላቀል የተዘጋጁት ፈረንሳዊውን ግብ ጠባቂ ኢላን ሜስሊየርን ነው።

ኢላን ሜስሊየር በሊድስ ዩናይትድ የነበረው ውል መጠናቀቁን ተከትሎ ከክለቡ የወጣ ሲሆን ሌላኛውን የእንግሊዝ ክለብ አርሰናል በነፃ ዝውውር ለመቀላቀል ከስምምነት ላይ ደርሷል።

ግብ ጠባቂ በኢላንድ ሮድ በነበረው የሰባት ዓመታት ቆይታው 215 ጨዋታዎችን ተሰልፎ አከናውኗል።

የ26 ዓመቱ ሜስሊዬር በቀጣይ የህክምና ምርመራውን አጠናቆ አርሰናልን የሚቀላቀል ከሆነ ከሁለቱ ስፔናዊያን ግብ ጠባቂዎች ዳቪድ ራያ እና ኬፓ አሪዛባላጋ ጋር ለቋሚ ተሰላፊነት ይፎክራል ተብሎ ይጠበቃል።

ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ